19/08/2026
ዛሬ በቀን 13/12/2018 ዓም በሀዋሳ ከተማ ባህል አደራሽ ክ/ከተማ አስተዳደር " በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በወጣቶችና በሴቶች እየተተገበረ ባለው የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች አንዱ የሆነው የወጣቶች በጎነትን በሆሰፕታል ተግባር በሀዋሳ አዳሬ ሆስፕታል በመገኘት ተከናውኗል።
በዝህ መረሃ ግብር ህመሟንን የመጠየቅ ተግባር ከመፈፀምም ባሻገር ወጣቶቹ አቅማቸው የቻለውን ፤ ለህመሟኑ የሚያስፈለሰጋቸውን ፈሳሾችንን የንፅህና መጠበቅያ ቁሳቁሶችን ጭምር የማድረስ ስራ ሰርተዋል።
በቦታው በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የሀዋሳ ከተማ ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ እና የሆስፕታሉ የቦርድ አባል የሆኑት ክብርት ፍሬህወት ወ/ፃድቅ ወጣቶች በራሳቸው ተነሳሽነት ግብአቶችን በማሰባሰብ የተቸገሩትን፤የታመሙትን እና ጠያቂ ያጡ ህመሟንን የመጎብኘታቸው ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የማህበረሰብን እሴት የሚገነባ ተግባር እንደሆነ ገልፀው ትርፉ የህልውና እርካታ ከመሆንም ባሻገር ከፈጣር የሚገኝ በረከትም እንዳለ በማንሳት ምስጋናቸውን ለወጣቶቹ አቅርበዋል።
በመረሃ ግብሩ ላይ የባህል አደራሽ ክ/ከተማ የማህበራዊ ክላስተር አመራሮች እና የበጎ ፍቃደኛ ወጣት አደረጃጀቶች እና ሴቶች ተገኝተዋል።