26/01/2026
የመጽሐፍ ምርቃት
📚 ከ11 ዓመታት በፊት ዓለምን ያስደነገጠው የሊቢያው ግድያ... እሱ እንዴት ተረፈ?
"ጓደኞቹ በISIS ሲያዙ እሱ እንዴት ቀረ? በእድል? በምክንያት? ወይስ በአጋጣሚ?"
| ከአዲስ አበባ እስከ መተማ፣ ከሱዳን እስከ ሊቢያ በረሃ... የሞት እና የሽሽት ጉዞ!
"ሃያ ሦስት" የተሰኘው የዳንኤል አብርሃ አዲስ መጽሐፍ፤ በወቅቱ የነበረውን የሊቢያን ሰቆቃ፣ የደላላዎቹን ሴራ እና የመጋዘኖቹን ጉስቁልና ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ
📖 ሰቆቃ እና ተአምር:
ጓደኞቹ ለሞት ሲነዱ፤ እሱ እንዴት ሊተርፍ ቻለ?
📖 የባሕር ላይ ውጣ ውረድ:
ሊቢያን አልፎ በጀልባ ለማቋረጥ ሲሞክር ምን ገጠመው?
📖 የአውሮፓ እውነት:
የከፈለው መስዋዕትነት የሚመጥን ካሳ በአውሮፓ አገኘ? ወይስ ሌላ ተጋድሎ?
ይህ መጽሐፍ ስለ እጣ-ፈንታ፣ ስለ ስኬት፣ ስለ ጽናት እና ተስፋ መቁረጥ አዲስ እይታን የሚሰጥ ነው።
የገጽ ብዛት - 262
ይዘት - የገዞ ማስታወሻ
26 ምዕራፎች አሉት
ደራሲ - ዳንኤል አብርሃ
አርታኢ እና አሰናኝ - ቢኒያም አቡራ
የፊታችን አርብ ሁላችንም ተገኝተን እንመርቀው!
📅 ቀን: አርብ ጥር 22 ቀን 2018ዓ.ም
📍 ቦታ: ዋልያ መጻሕፍት (4 ኪሎ፣ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ፣ ኢክላስ ሕንጻ፣ 4ኛ ፎቅ)
የማይረሳ ታሪክ፣ የማይቀር ምርቃት!