Ataye City Government Communication office

Ataye City Government Communication office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ataye City Government Communication office, Government Organization, Ataya, Shewa, Ataya.

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" በሚል መሪ ቃል 10 ደርዘን ደብተር ለመግዛት አቅም ለሌላቸው  ተማሪዎች ድጋፍ አደረጉ።አጣዬ፣ ሐ...
18/07/2026

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" በሚል መሪ ቃል 10 ደርዘን ደብተር ለመግዛት አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ድጋፍ አደረጉ።

አጣዬ፣ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ፣ የ2019 የትምህርት ዘመንን አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት እንዳይቸገሩ በማለት ዘመቻውን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል።

መጪው የትምህርት ዘመን በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ያለባቸውን ተማሪዎች ለመደገፍ "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" በሚል መሪ ቃል 10 ደርዘን ደብተር በመግዛት በዛሬው ዕለት አስረክበዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባ እንደተናገሩት " በጎነት የማህበረሰብን አብሮነት እና መተሳሰብ የሚያጠናክር ከፍተኛ እሴት መሆኑን ገልጸው፣ ይህ የድጋፍ ዘመቻ በሌሎችም አካላት በስፋት እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በመሆኑም የከተማው ተቋማት ኃላፊዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ባለሀብቶች፣ የንግድ ማህበረሰብ እና መላው የአጣዬ ከተማ ነዋሪዎች "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" የሚለውን ዘመቻ በመቀላቀል አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

በሰሜን ሸዋ ዞን "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" የበጎ አድራጎት ዘመቻ በሁሉም ወረዳዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ​አጣዬ ፦ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም(አጣዬ ኮሙኒኬሽን )የ2019...
18/07/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" የበጎ አድራጎት ዘመቻ በሁሉም ወረዳዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

​አጣዬ ፦ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም(አጣዬ ኮሙኒኬሽን )

የ2019 የትምህርት ዘመንን ሁሉም ተማሪዎች በተሟላ የመማሪያ ቁሳቁስ እንዲጀምሩ ለማስቻል የተጀመረው "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" የበጎ አድራጎት ዘመቻ በሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች በላቀ ደረጃ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የዞኑ ትምህርት መምሪያ አሳሰበ

​መምሪያው ባስተላለፈው ጥሪ፤ የፊታችንን የትምህርት ዘመን ስኬታማ ለማድረግ የመንግስት አመራሮች፣ መምህራን፣ የዘርፉ ሠራተኞች፣ ወላጆች፣ ባለሀብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የልማት አጋሮችና መላው ህብረተሰብ በንቃት በመሳተፍ ለተማሪዎች የደብተር ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቋል።

​በዚሁ የድጋፍ መድረክ ላይ የተገኙት የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ እንግዳወርቅ፤ 10 ደርዘን (120) ደብተሮችን ለመለገስ ቃል በመግባት ለአካባቢው አመራሮችና ለማህበረሰብ ክፍሎች አበረታች አርአያነት አሳይተዋል።

​ዘመቻው በሁሉም ወረዳዎች በተቀናጀና በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ያሳሰበው መምሪያው፤ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች አቅማቸው በፈቀደው መጠን በመሳተፍ የተማሪዎችን የትምህርት ጅምር እንዲደግፉ ጥሪውን አቅርቧል።

"ዛሬ የምናደርገው ድጋፍ የነገውን ትውልድ ይገነባል" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ንቅናቄ የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባም ተመላክቷል።
መረጃው ሰሜን ሸዋ ኮሙኒኬሽን

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ G+2 የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ እንዲቀጥል በዛሬው እለት  ቦርዱ ውሳኔ ማስተላለፉን ተገለፀ።አጣዬ፣ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) – በአጣዬ ፖሊ ቴ...
18/07/2026

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ G+2 የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ እንዲቀጥል በዛሬው እለት ቦርዱ ውሳኔ ማስተላለፉን ተገለፀ።

አጣዬ፣ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) –

በአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በበጀት እጥረት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የG+2 የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ እንዲቀጥል የኮሌጁ ቦርድ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ ውሳኔ አሳልፏል።

በስብሰባው ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ እንድሪስ ሰይድ ለቦርዱ ባቀረቡት ሪፖርት፣ የተማሪዎችን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍ በአጣዬ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) እና በኤፍራታና ግድም ወረዳ በጋራ ሊገነባ የታቀደው ሕንፃ በበጀት እጥረት ምክንያት ሥራው መቋረጡን ገልጸዋል። በመቋረጡም ያልተጠናቀቀው ግንባታ ለብልሽት እየተጋለጠ መሆኑን አስረድተዋል።

የቦርዱ አባላት በቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት በማካሄድ አስተያየታቸውን ካቀረቡ በኋላ፣ ግንባታው በአፋጣኝ እንዲቀጥል ውሳኔ ሰጥተዋል።
የአጣዬ ከተማ ከንቲባና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ተስፋ በበኩላቸው፣ ለተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የቆየው የመማሪያ ሕንፃ ግንባታ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ሥራ እንዲገባ እንደተወሰነ ገልጸው፣ የከተማ አስተዳደሩም የበኩሉን ኃላፊነት በመወጣት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ቦርዱ፣ ኮሌጁ ለአጣዬ ከተማ፣ ለኤፍራታና ግድም ወረዳ፣ ለጅሌ ጥሙጋ ወረዳ፣ ለሰንበቴ ከተማ እና ለአካባቢው ህብረተሰብ የትምህርትና የሙያ ስልጠና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተቋም በመሆኑ፣ የግንባታው ሥራ እንዲጠናቀቅ በገንዘብም ሆነ በቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ የሚችሉ አካላት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል።

በሰሜን ሸዋ ዞን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እና  የአረርቲ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አመራር እና ሚኒ ካቢኔ አባላት በተገኙበት በቀጠናው  ሰላም እና ፀጥታ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።የውይይቱን ...
18/07/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እና የአረርቲ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አመራር እና ሚኒ ካቢኔ አባላት በተገኙበት በቀጠናው ሰላም እና ፀጥታ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።

የውይይቱን መድረክ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻ ኮማንዶ እዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ እና የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ኤልያስ አበበ የመሩት ሲሆን።

በውይይቱ መድረክ ላይ አቶ ተክለየስ በለጠ የሰ/ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የሪፐብሊካን ጋርድ ጥበቃ ሃይል አዛዥ ብ/ር ጀነራል አካሉ፣ የልዩ ዘመቻ ምክትል አዛዥ ብ/ጀነራል አበባው ሰይድ እና የሪፐብሊካን ጋርድ ጥበቃ 5ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ፍቃዱ ጥላሁን እንዲሁም አቶ ይደሰቱ ክፈተው የሰ/ሸዋ ዞን ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ እና የክፍለ ጦሩ ሌሎች አመራሮች መሳተፍ ችለዋል።

በመጨረሻም በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩን ማጠቃለል ተችሏል።

•~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊
•~•~•

የአጣዬ ከተማ ምክር ቤት አባላት 11,322 ብር ለክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራ ድጋፍ አደረጉ።አጣዬ፣ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) – የአጣዬ ከተማ ምክር ቤት 46ኛውን መደበኛ...
17/07/2026

የአጣዬ ከተማ ምክር ቤት አባላት 11,322 ብር ለክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራ ድጋፍ አደረጉ።

አጣዬ፣ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) –

የአጣዬ ከተማ ምክር ቤት 46ኛውን መደበኛ ጉባኤ በማጠናቀቅ አባላቱ ለክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራ የሚውል 11,322 ብር በማሰባሰብ ድጋፍ አድርገዋል።

የድጋፍ ገንዘቡን የአጣዬ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ መሰረት አካሉ ለአጣዬ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ወጣቶች ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ጌጤነሽ ማሞ በዛሬው ዕለት አስረክበዋል።

በድጋፉ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ ገንዘቡን የተረከቡት ወይዘሮ ጌጤነሽ ማሞ፣ የምክር ቤቱ አባላት ላደረጉት ሰብዓዊ ድጋፍ ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የተሰጠው ድጋፍ በክረምቱ ወቅት ለሚከናወነው የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ጥገና እና ገንዘብ ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች እንደሚውል ገልጸው፣ ለዚህ ተግባር የተሳተፉትን የምክር ቤት አባላት በድጋሚ አመስግነዋል።

የዝናብ ስርጭት ከአየር ንብረት ለዉጥ ጋር ተያይዞ  ያለውን ስጋት  ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸአጣዬ ፤ ሀምሌ 10 ቀን 2018ዓ.ም (አጣዬ ኮሙኒኬሽን )የሰ...
17/07/2026

የዝናብ ስርጭት ከአየር ንብረት ለዉጥ ጋር ተያይዞ ያለውን ስጋት ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ

አጣዬ ፤ ሀምሌ 10 ቀን 2018ዓ.ም (አጣዬ ኮሙኒኬሽን )

የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ በዞኑ የሚገኙ አርሶ አደሮች የዝናብ እጥረትን እና የተዛባ የዝናብ ስርጭትን መቋቋም እንዲችሉ የቅድመ መረጃ የመስጠትና የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ታደሰ ማሙሻ እንደገለጹት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰተው የኢሊኖ ክስተት በዞኑ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅዕኖ ለመቀነስ የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተቀርጸው እየተተገበሩ ይገኛሉ።

ኃላፊው በጥናት ሪፖርቶች ላይ ተመስርተው ኢትዮጵያ በተቆራረጠ የዝናብ ስርጭት እና በጎርፍ ስጋት ላይ እንደምትገኝ አስረድተዋል።

ይህንኑ ተከትሎ በሰሜን ሸዋ ዞን ስር በሚገኙ 24 የግብርና ወረዳዎች እና ወደ 373 በሚጠጉ ቀበሌዎች ላይ የክትትል ስራ እየተሰራ ይገኛል። እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት 55 ቀበሌዎች መካከለኛ እና 184 ቀበሌዎች ደግሞ አነስተኛ ዝናብ ያገኙ ሲሆን፣ 102 ቀበሌዎች ደግሞ እስካሁን ምንም ዓይነት ዝናብ አላገኙም።

ይሁን እንጂ በዞኑ ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን እና አካባቢው ከሌሊት ጀምሮ ጥሩ ዝናብ እየጣለ በመሆኑ በሀምሌ ወር የተሻለ የዝናብ ስርጭት ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኃላፊው ጠቁመዋል።

የዝናብ እጥረቱን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት ከተቀረጹት ስልቶች መካከል ዝናብ እንደመጣ አርሶ አደሩ ፈጥኖ ወደ ዘር ስራ እንዲገባ ማድረግ፣ የመስኖ ቦዮችን በማጽዳት መስኖን እንደ ደጋፊ አማራጭ መጠቀም፣ ፈጥነው የሚደርሱ፣ በሽታና ድርቅን የሚቋቋሙ የምርጥ ዘር ዝርያዎችን መጠቀም፣ ውሃ የማቆር ስራዎችን መስራት እና አነስተኛ የውሃ አማራጮችን በበጀት አስደግፎ መቆፈር እና የእንስሳት መኖ እጥረትን አስቀድሞ ማቀድና ማዘጋጀት ይገኙበታል ብለዋል።

በተጨማሪም መምሪያው መንግስታዊ ካልሆኑ (NGOs) እና ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት አጠቃላይ እቅዶችን በድጋሚ የመከለስ እና ምርጥ ዘሮችን የማቅረብ ስራ እያከናወነ ይገኛል።

አሁኑ ወቅት ከ34 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ተዘጋጅቶ ለወረዳዎች እየተሰራጨ መሆኑንና አርሶ አደሩ በልማት ቡድን ተደራጅቶ ወደ ስራ እንዲገባ እየተደረገ መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
ሰሜን ሸዋ ኮሙኒኬሽን

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን የ4ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸምን ከጠቅላላ አመራሩ ጋር ገመገመ።አጣዬ፣ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) – የአጣዬ ከተማ...
17/07/2026

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን የ4ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸምን ከጠቅላላ አመራሩ ጋር ገመገመ።

አጣዬ፣ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) –

የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን በኃላፊዋ ወ/ሮ ኤልሳቤት ከበደ አስተባባሪነት የ2018 ዓ.ም. 4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም፣ የሱፐርቪዥን ግብረ መልስ እና የፓርቲ ግብረ መልስ ግምገማ ከጠቅላላ የከተማው አመራር ጋር አካሂዷል።

በግምገማው የአጣዬ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስ፣ የከተማው ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፍ እንዲሁም ሌሎች የከተማው አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ኮሚሽን ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤት ከበደ የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸምና የሱፐርቪዥን ግብረ መልስን በዝርዝር በማቅረብ በተሳታፊዎች አስተያየትና ግብረ መልስ ተሰጥቶበታል። በመቀጠልም ከቀረበው ሪፖርት በመነሳት የፓርቲ ግብረ መልስ ለብልፅግና ቤተሰብ ቀርቧል።

በመጨረሻም አቶ ከድር እንድሪስ እና ወ/ሮ ኤልሳቤት ከበደ በሪፖርቱ ላይ ከተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት ግምገማውን አጠናቀዋል።

በበጀት ዓመቱ ጥሩ የሥራ አፈጻጸም ላሳዩ ከጠቅላላ አመራሩ መካከል ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ ቤተሰቦች ዕውቅናና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

"ከባህላዊ አሠራር ወደ ዲጂታል ሽግግርና ሁለንተናዊ የሪፎርም ስኬቶች ማከናወኑን መምሪያው አስታወቀ"​አጣዬ ፦ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (አጣዬ ኮሙኒኬሽን ) በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞ...
16/07/2026

"ከባህላዊ አሠራር ወደ ዲጂታል ሽግግርና ሁለንተናዊ የሪፎርም ስኬቶች ማከናወኑን መምሪያው አስታወቀ"

​አጣዬ ፦ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (አጣዬ ኮሙኒኬሽን )

በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን የሰው ሀብት ልማት መምሪያ፦ ከባህላዊ አሠራር ወደ ዲጂታል ሽግግርና ሁለንተናዊ የሪፎርም ስኬቶች ማከናወኑን ገልጿል።

መምሪያ የዜጎችን እርካታ ለማረጋገጥና የመንግሥት አገልግሎትን ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂ ለማድረግ ያስቻሉ የሪፎርም ምሰሶዎችን ይፋ አድርጓል።

በበጀት ዓመቱ በመልካም አስተዳደር፣ በአቅም ግንባታ፣ በሲቪል ሰርቪስ ዲጂታላይዜሽን እና በአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ላይ ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገቡን የመምሪያው የሰው ሀብት አስተዳደር ቡድን መሪና የመምሪያ ኃላፊ ተወካይ በሆኑት በአቶ ተሾመ ሸዋየ ገልጸዋል።

​መምሪያው በዞኑ ሲስተዋሉ የነበሩ የሠራተኞችና የዜጎች ቅሬታዎችን በይፋ ለይቶ መፍትሔ በመስጠት ረገድ ሰፊ ርምጃዎችን ወስዷል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ ከዞን መምሪያ ጀምሮ እስከ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ድረስ የተለዩ 2 መቶ 3 መቶ 31 የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሙሉ በሙሉ መፈታታቸውን ገልጸዋል።

በዞን ደረጃ የተለዩ 21 የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችም በተመሳሳይ ሙሉ በሙሉ ምላሽ አግኝተዋል ያሉት አቶ ተሾመ

የውጤት ተኮር አሠራር መዛባት ፣ የትምህርትና ሥልጠና ዕድሎች ፍትሐዊዊነት ማጣት ፣ የዝውውርና ምደባ ግልጽነት መጓደል

በሠራተኛው ዘንድ ቅሬታ የሚፈጥሩ የዝውውርና የምደባ አሠራሮች ግልጽነት ባለው መንገድ እንዲመሩ መደረጉን አንስተዋል።

​የአቅም ግንባታና የሠራተኞች ተጠቃሚነት በተመለከተ የተቋማት ውጤታማነት የሚወሰነው በበቃ የሰው ኃይል በመሆኑ፣ መምሪያው ለአጭርና ረጅም ጊዜ ሥልጠናዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መሥራቱን ገልጸዋል።

በዞኑ ያሉ 1ሺህ 7 የመንግሥት ሠራተኞች በግብርና፣ በጤና፣ በእንስሳት ሀብትና በኅብረት ሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሙያዎች በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲና በተለያዩ ተቋማት አማካኝነት ከዲግሪ እስከ ማስተርስ የረጅም ጊዜ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ ለ12 ሺህ 3 መቶ 30 ሠራተኞች የእውቀት፣ የአመለካከትና የክህሎት ክፍተቶቻቸውን ለመሙላት የሚያስችል የአጭር ጊዜ ሥልጠና ወስደዋል።

​የመረጃ ደኅንነትና የዲጂታላይዜሽን ሽግግርን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ ከባህላዊ አያያዝ ወደ ዘመናዊ ዲጂታል ሥርዓት ማሸጋገር ሌላው የመምሪያው ትልቅ ስኬት ነው።

​በተለይም በ2014 ዓ.ም በነበረው የሰሜኑ ጦርነት ምክንያት እንደ መሐል ሜዳ እና አጣዬ ባሉ ከተሞች የመንግሥት ሠራተኞች የግል ማህደርና ሰነዶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ያስታወሰው መምሪያው፤ ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ መረጃዎችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ከወረዳና ከተማ አስተዳደር እስከ ክልል ድረስ ያለውን የወረቀት ንክኪን በከፍተኛ ደረጃ ማቋረጥ ተችሏል።

የዲጂታል ተጠቃሚነት፦ በአሁኑ ወቅት 21 ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሠራተኞቻቸውን መረጃ ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ አድርገው አጠናቀዋል ብለዋል።

የቀሩት 10 አካባቢዎችም ከበጀት ጋር የተያያዙ ችግሮቻቸው ተቀርፈው ወደ ሥርዓቱ እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል።

​የሪፎርም ሥራዎችና የ“ሞሰብ” (አንድ ማዕከል) አገልግሎት
​መምሪያው የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል መመሪያ ቁጥር 48 እና 49ን መሠረት በማድረግ በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን ተግባራዊ ተደርገዋል ብለዋል።

​የ"ሞሰብ" (አንድ ማዕከል) አገልግሎት መስፋፋት፦ ዜጎች ፈጣንና የተቀናጀ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችለው ይህ አሠራር በቡልጋ፣ በአረርቲ እና በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደሮች በስኬት ተጀምሯል።

በተለይም በቡልጋና በሸዋሮቢት ፈጣን ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሲሆኑ በአረርቲም በ9 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

​በተጨማሪም በአዋጅ ቁጥር 309/2018 መሠረት የሠራተኞችን ግንዛቤ የማሳደግና ተቋማት በሕግና በታማኝነት እንዲመሩ የማድረግ ሥራዎች ተከናውነዋል።

​​በሪፎርምና በቅጥር ሥራዎች ውስጥ የአካታችነት መርህን ለመተግበር በተደረገው ጥረት፦በተከናወኑት የቅጥርና ስምሪት ሥራዎች ውስጥ የሴቶች ድርሻ 73 ነጥብ 18 በማድረስ ረገድ ሰፊ ስኬት ተመዝግቧል።

የወጣቶች ተሳትፎ በሥልጠናና በተለያዩ መድረኮች 70 ፐርሰንት መድረስ ቢችልም የአካል ጉዳተኞች ቀጥተኛ ተጠቃሚነት አሁንም ክፍተት ያለበት በመሆኑ፣ በቀጣይ ሊታረም እንደሚገባ ተገልጿል።

​በማጠቃለያው፣ የሰሜን ሸዋ ዞን የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ተግባራት የመንግሥት ሠራተኛውን አቅም ከመገንባት ባለፈ፣ ዜጎች የሚፈልጉትን ፈጣንና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ጠንካራ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተመልክቷል።

‎​የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም መገምገሙ ተገለፅ።‎  አጣዬ ፦ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም(አጣዬ ኮሙኒኬሽን )‎‎​ኮሌጁ በዛሬው እለት የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህ...
16/07/2026

‎​የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም መገምገሙ ተገለፅ።

‎ አጣዬ ፦ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም(አጣዬ ኮሙኒኬሽን )

‎​ኮሌጁ በዛሬው እለት የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራኖች እና የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት በ2018 በጀት አመት የተከናወኑ የ12 ወራት ስራ አፈፃፀሙን ገምግሟል።

‎ የኮሌጁ ዲን አቶ እንድሪስ ሰይድ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በዚህም ከሚቀርበው ሪፖርት በመነሳት በቀጣይ በጀት አመት ከዚህ የበለጠ ሰርተን ኮሌጃችንን ወደፊት ከፍ ማድረግ አለብን ሲሉ ለአጠቃላይ ሰራተኛው ግንዛቤ በመፍጠር ውይይቱን አስጀምረዋል።

‎የስራ አፈፃፀም ሪፖርቱ በኮሌጁ የእቅድና በጀት ዝግጅት ባለሙያ በወ/ሮ በለጠች ምኒሉ በየቡድኑ በዝርዝር ቀርቧል።

‎ ​በመቀጠል የውይይት መድረኩ በኮሌጁ ዲን አቶ እንድሪስ ሰይድ፣ በም/ዲን አቶ አረጋኸኝ ጌታቸው እና ወ/ሮ ባንችአምላክ አዳነ የተመራ ሲሆን ከቀረበው ሪፖርት በመነሳት ከተሳታፊዎች በጥንካሬ ወይም በድክመት ሀሳቦች ቀርበዋል። ከቀረቡት ሀሳቦች መካከል በጥንካሬ የተነሱትን ማስቀጠል እንዲቻል በማሳሰብ ድክመቶችና በተነሱ ጥያቄዎች ዙሪያ ጉዳዩ ከሚመለከታቸውና ባለሙያዎችና ከመድረክ አመራሮች ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት ውይይት ተደርጓል።


‎በአጠቃላይ አቶ እንድሪስ ውይይቱን ሲያጠቃልሉ የዚህ አመት ስራችን እጅግ በጣም ጥሩ የነበረና ኮሌጁን ይበልጥ ውጤታማ ያደረጉ ስራዎች የተሰሩበት በጀት አመት እንደነበረ ገልፀው በቀጣይ ስራዎቻችን ላይ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ክረምት በችግኝ ተከላና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን እንዲሰራ በማለት መግባባት ላይ ተደርሶ ውይይቱ ተጠናቋል።

‎መረጃው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ነው

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ20ኛ ጊዜ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።አጣዬ፣ ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) – በአጣዬ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው አንጋፋው ...
16/07/2026

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ20ኛ ጊዜ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።

አጣዬ፣ ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) –

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው አንጋፋው የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ20ኛ ጊዜ የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቋል።

ኮሌጁ በደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠና ሲሰጣቸው የቆዩ ተማሪዎችን በሐምሌ 12/2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 20ኛው ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚያስመርቅ ገልጿል። ለዚህም የምረቃ ፕሮግራም አስፈላጊ የሆኑ ሁሉንም ዝግጅቶች መጠናቀቃቸው ተገልጿል።

ይህ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ኮሌጁ በአጣዬ ከተማና በአካባቢው የብቁ የሙያ ባለሙያዎችን በማፍራት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ በግልጽ የሚያሳይ መድረክ መሆኑም ተጠቁሟል።

ኮሌጁ በሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ለረጅም ዓመታት ያከናወነው ሥራ በአካባቢው የሰው ኃይል ልማትን በማጠናከርና ለሥራ ገበያ ዝግጁ የሆኑ ባለሙያዎችን በማፍራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱም ይገለፃል።

መረጃውን ከአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት።

Address

Ataya, Shewa
Ataya
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ataye City Government Communication office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share