Asosa Town Administration Revenues Department

Asosa Town Administration Revenues Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Asosa Town Administration Revenues Department, Government Organization, Asosa.

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በ11 ወር ውስጥ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ 1,370,612,553.14 ብር ሰበሰበ።*******ሰኔ( አሶሳ 04/11/18 ዓ.ም)የአሶሳ ከተማ አስተዳደር...
11/06/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በ11 ወር ውስጥ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ 1,370,612,553.14 ብር ሰበሰበ።
*******
ሰኔ( አሶሳ 04/11/18 ዓ.ም)
የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ 1,308,714,901.81ለመሰብሰብ አቅዶ 1,370,612,553.14 በመሰብሰብ እቅዱን 100% በላይ ማሳካት ተችሏል።

እቅዱን ማሳካታችን እጅግ በጣም አመርቂ ቢሆንም ከተማው ካለው የመሰረተልማት ፍላጎትና ስፋት አንፃር በቂ ስላልሆነ በቀሪው ትቂት ወራቶች አቅማችን አሟጠን ከዚህ በላይ በመስራት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ያስፈልጋል ሲሉ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አንዋር አስር ገልፀዋል።

ለእቅዳችን መሳካት ከጎናችን የነበሩትን ባለድርሻ አካላት ማመስገን ይገባል ያሉት አቶ አንዋር አስር በሰኔ ወር የሚሰሩ ስራዎች ቼክ ሊስቱን ገምግመው የስራ አቅጣጫ/ እና ሰምሪት ሰጥቷል።

የአሶሳ ከተማ አሰ/ር  ግብር ከፈዮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት በተደረገው ቅስቀሳ በከተማችን የሚገኙ ግብር ከፍዮች የመክፈያ ጊዚያቸውን ጠብቀው በመክፈል ላ...
05/06/2026

የአሶሳ ከተማ አሰ/ር ግብር ከፈዮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት በተደረገው ቅስቀሳ በከተማችን የሚገኙ ግብር ከፍዮች የመክፈያ ጊዚያቸውን ጠብቀው በመክፈል ላይ መሆናቸውን የአሶሳ ከተማ አሰ/ር ገቢዎች መምሪያ አሰታወቀ ።
****
(ግንቦት 28/2018 ዓ/ም )የአሶሳ ከተማ አሰ/ር ግብር ከፈዮች በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት በተደረገው ቅስቀሳ ደረጃ''ሀ''ንና በወረዳ አንድንና ወረዳ ሁለት ስር ያሉትን የደረጃ ''ለ'' ግብር ከፋዮችን ጨምሮ የመክፈያ ጊዚያቸውን ጠብቀው በመክፈል ላይ መሆናቸው የአሶሳ ከተማ አሰ/ር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊና ከፍተኛ ባለሞያዎች ባደረጉት የመሰክ ምልከታ የከተማው ግብር ከፋይ ማህበርሰብ ለአዋጁ ተፈፃሚነት ተገዥ መሆናቸውን የሚያመላክት መሆኑን የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አንዋር አስር ገልፀዋል:: ከዚህም በተጨማሪ በከተማችን ያለችሁ የድርጅትና መኖሪያ ሁሉም ባለይዞታዎች ያለባቸውን የአፈር ግብር ወቅቱን ጠብቀው እንዲከፍሉ እናሳስባለን።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

04/06/2026

ማስታወቂያ ለአሶሳ ከተማ የድርጅትና መኖሪያ ባለይዞታዎች በሙሉ=-
የአፈር:የጣሪያና ግርግዳ ውዝፍ ግብር ያለባችሁና የ2018ን ያልከፈላችሁ ባለይዞታዎች አላስፈላጊ ቅጣትና ወለድ ውስጥ ከመግባታችሁ በፊት በወቅቱ መጣችሁ እንድትከፍሉ ስንል እናሳስባለን።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከሁለቱ የከተማ አስተዳደር ወረዳዎች ሃላፊና ማኔጅመንት አባላት ጋር በጋራ በመሆን የሚያዚያ ወር ሪፖርትን በመገምገም ለቀጣይ ግንቦት ወር ለሚሰሩ ስራ...
12/05/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከሁለቱ የከተማ አስተዳደር ወረዳዎች ሃላፊና ማኔጅመንት አባላት ጋር በጋራ በመሆን የሚያዚያ ወር ሪፖርትን በመገምገም ለቀጣይ ግንቦት ወር ለሚሰሩ ስራዎች ስምሪት ሰጠ።
******************
ግንቦት 04/09/10 ዓ.ም
ገቢዎች መምሪያው ከሁለቱ ወረዳዎች ጋር በመሆን በሚያዚያ ወር የተሰሩ የተቋም ስራዎችንና በጋራ ስምሪት የተሰሩ ስራዎችን በጋራ ገምግመዋል

እንደተቋም ከተማ አስተዳደሩ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ የሚሰበስባቸው ገቢዎች ለጋራ አላማና የከተማ አስተዳደሩን ገቢ በማሳደግ የከተማውን መሰረተልማት ማፋጠን እስከሆነ ድረስ በጋራ የተሰሩ ስራዎችን ገምግሞ ከፍተቶችን የጋራ በማድረግ መስራቱ ገቢያችንን የሚያሳድግ ተግባር ስለሆነ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አንዋር አስር አሳስበዋል።

በመሆኑም በሚያዚያ ወር የተሰሩ የጋራ ስራዎች አመርቂ ቢህንም ያሉ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ገቢ መሰብሰብ አስፈላጊ ስለሆነ ለቀጣይ ግንቦት ወር ለሚሰሩ ስራዎችም ስምሪት በመስጠት ወይይታቸውን አጠናቀዋል።

''ገቢ ለልማት''

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የገቢ አሰባሰብ ሂደት ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ እንደሆነ ተገለጸ።‎***********************‎ ሚያዝያ 29/2018 ዓ/ም አሶሳ፣ በአሶሳ ...
07/05/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የገቢ አሰባሰብ ሂደት ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ እንደሆነ ተገለጸ።
‎***********************
‎ ሚያዝያ 29/2018 ዓ/ም አሶሳ፣ በአሶሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ የሽያጭ ማሽን ትግበራ መጀመሩን አስታወቀ።

‎እንደ አሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ አንዋር አሲር ገለጻ ዲያንካ ንግድ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለሽያጭ ባቀረባቸዉ ካሽ ሪጂስተር ማሽኖች ቢያንስ ሁለት መቶ የሚሆኑ ነጋዴዎች ተለይተዉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

‎የገቢ አሰባሰብ ሂደት ባለመዘመኑ ከተማ አስተዳደሩ የሚገባውን ገቢ ሲሰበስብ አልነበረም ያሉት አቶ አንዋር አሲር ይህንን ለመቅረፍ ታስቦ እነደሆነ ገልጸዋል።

‎የሽያጭ ማሽኑ ከዚህም በተጨማሪ ለደረሰኝ ህትመት ይወጣ የነበረን ወጭ ይቆጥባል፣ተገልጋዩን ከመጉላላት እንደሚታደግ እና የታክስ ስወራ ይከላከላል በማለት ማሽኑን ሲረከቡ ያነጋገርናቸዉ ተገልጋዬች ገልጸዋል።

‎''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''



የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ2018 ዓ/ም የዘጠኝ ወር የገቢ አፈጻጸም‎  1,157,455,603.62  መሆኑን አሳወቀ።‎***********************************...
14/04/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ2018 ዓ/ም የዘጠኝ ወር የገቢ አፈጻጸም‎ 1,157,455,603.62 መሆኑን አሳወቀ።
‎**************************************************

‎ሚያዝያ 06/2018 ዓ/ም አሶሳ፣
‎የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የመምሪያው ማኔጅመንት አባላት እና የሁለቱም ወረዳዎች አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት የዘጠኝ ወር የገቢ አፈጻጸም ሪፖርትር ቀርቦ ተወያይተውበታል።

በግምገማው ወቅት መድረኩን የመሩት የአሶሳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ አንዋር አሲር ገቢ ለሀገር ኢኮኖሚ መበልፀግና ለሁለንተናዊ የልማት ስራዎች መከናወን ወሳኝ መሆኑን አስታውሰው የከተማችን የንግድ እንቅስቃሴ ከግዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ይህንን የንግድ እንቅስቃሴ በደንብና አዋጅ ስር በማስተዳደር ለከተማችን የገቢ እድገት ግብር ከፋይ ማህበረሰብ እና ገቢ ሰብሳቢ ባለሙያዎች የተጣለባቸውን ሀላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

‎በዘጠኝ ወር አፈጻጸም 1,023,924,438.86 ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 1,157,455,603.62 (አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ ሀምሳ ሰባት ሚሊዮን አራትመቶ ሀምሳአምስት ሺ ስድስት መቶ ሶስት ብር ከስልሳ ሁለት ሳንቲም) ገቢ መሠብሠብ መቻሉን በቀረበው ሪፖርትር አሳውቀዋል።

‎ከዚሁ ከተሰበሰበው ገቢ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ 48.20% ሲሆን የወረዳ ሁለት ገቢ 26%፣ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ይወሰዳል አንድ ገቢ 25.80% ድርሻ እንዳላቸው ተመላክቷል።

‎በቀሪው ሩብ አመት ከሁለቱም ወረዳ ጋር በመቀናጀት ቼክ ሊስት ተዘጋጅቶ ባለሙያዎችን ስምሪት በመስጠት በተሻለ መልኩ ለመሰብሰብ ጥረት እየተደረገ እንደሆነ የገለጹት የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዋር አሲር ከነበረው አሁን ያለበት የገቢ አሰባሰብ ሂደትም እየተሻሻለ መሆኑንም ገልጸዋል።

የሁለቱም ወረዳ አመራሮች በበኩላቸው በተዘጋጀው ቼክ ሊስት መሰረት ለተሻለ ገቢ በትጋት እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከተመረጡ የደንብ አስከባሪወችና የክትትል ባለሙያዎች ጋር ውይይት አደረገ።**መጋቢት 30/07/18 ዓ.ምየአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ለ15...
08/04/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከተመረጡ የደንብ አስከባሪወችና የክትትል ባለሙያዎች ጋር ውይይት አደረገ።
**
መጋቢት 30/07/18 ዓ.ም
የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ለ15 ቀን በሚሰሩ የስራ ስምሪት ላይ አዋጁን በተመለከተ ውይይት ተደርጓል።
ከዚህም በተጨማሪ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አንዋር አስር ለቀጣይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ደንቦችና የክትትል ባለሙያዎች በመናበብና በጋራ በመሆን ህገዎጦችን የማስተካከልና የማረም ስራ እንዲሰራ ሲሉ በአፅንኦት አሳስበዋል።
**ገቢ ለልማት**

*ዛሬ መጋቢት 21/2018 ዓ/ም የአሶሳ ከተማ አሰ/ር  ገቢዎች መምሪያ የመጋቢት ወር የ15 ቀናት የስራ ስምሪት ሪፖርት ከሁለቱም ወረዳዎች ጋር በመሆን የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ በሚሰሩ ቀሪ ...
30/03/2026

*ዛሬ መጋቢት 21/2018 ዓ/ም የአሶሳ ከተማ አሰ/ር ገቢዎች መምሪያ የመጋቢት ወር የ15 ቀናት የስራ ስምሪት ሪፖርት ከሁለቱም ወረዳዎች ጋር በመሆን የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ በሚሰሩ ቀሪ ሥራዎች ላይም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የአሶሳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች መምሪያ በ2018 አ.ም የ8 ወርና የየካቲት ወር ብቻ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ 1.055.479.718,36 ሳንቲም) ገቢ መሰብሰቡን ገለፀ።*መጋቢት 8/2018 አ....
17/03/2026

የአሶሳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች መምሪያ በ2018 አ.ም የ8 ወርና የየካቲት ወር ብቻ ሁለቱን ወረዳዎች ጨምሮ 1.055.479.718,36 ሳንቲም) ገቢ መሰብሰቡን ገለፀ።
*
መጋቢት 8/2018 አ.ም ፤ የአሶሳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች መምሪያ የ2018 አ.ም የተጠናቀቀ የ8 ወር የገቢ አሰባሰብና ከቀጣይ እቅድ የየካቲት ወር የገቢ አሰባሰብ የስራ አፈፃፀም ሪፓርት ከሁለቱም ወረዳ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ጋር በጋራ ገመገመ።

በገቢ አሰባሰብ ሪፓርት ግምገማ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአሶሳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ አንዋር አሲር እንደገለፁት ገቢ የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በአዋጅና ደንብ የተደነገጉ የገቢ ግብርና ሌሎች ታክሶችን በተገቢው የአሰራር ስርዓት መሰረት መምራትና ማስተዳደር ይገባል በማለት የገቢ አሰባሰብና አስተዳደር ስርዓታችንን በማዘመን በጥብቅ ክትትልና በስኬታማ አመራርነት ውጤታማ ስራ መስራት ይቻላል። እንደ አሶሳ ከተማ አስ/ር ከዚህ ቀደም የነበረውን ዝቅተኛ የገቢ መጠን በማሻሻል ለመጀመሪያ ጊዜ በቢሊዮን የሚየሚቆጠር ገቢ መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል። ለስኬቱ ቁልፍ ጉዳዮች ተብለው የሚጠቀሱት የተሻሻለው የግብር አዋጅ በመከተል ከአመራር አስከ ታችኛው ባለሙያና መዋቅር ድረስ ተናበን መስራታችን እና ግብር ከፋይ ህብረተሰባችን ግብርን በወቅቱ የመክፈል ግንዛቤው እየጨመረ በመምጣቱ እንዲሁም የግብር ከፋይ ማህበረሰብ ቁጥር በመጨመሩ አፈፃፀማችንን የተሳካ እንዲሆን አድርጎታል ብለዋል።

አክለውም አቶ አንዋር በራሷ አቅም የበለፀገች ኢትዮጲያን ለመገንባት በምናደርገው ጥረት ገቢ ዋናውን ቦታ ስለሚሸፍን ቀጣይ አቅማችን አሟጠን በመጠቀም በቁርጠኝነት እንሰራለን በማለት በስራው ላይ አስተዋፆኦ ላበረከቱ አመራሮችና ስቼፍ ሰራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበው ቀጣይ ለተሻለ አፈፃፀም ተግተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።

የገቢ አሰባሰብ ስራ ከእቅዱ 103% ፐርሰንት መከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ለመሰብሰብ የታቀደው 920.785.242.21 ሳንቲም ሲሆን አፈፃፁሙ 1.055.479.718,36 (አንድ ቢሊዮን ሀምሳ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ አስራ ስምንት ብር ከሰላሳ ስድስት ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል።

ከ2017 አ.ም የገቢ አሰባሰብ እቅድ ጋር ሲነፃፀር 52.6 % እድገት አሳይቷል ተብሏል። የወረዳ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ገንቢ አስተያየት ሰጥተው ቀጣይ ለተሻለ ገቢ መገኘት የበኩላቸውን ሙያዊ ግድታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ማስታወቂያ:-ለአሶሳ ከተማ ግብር ከፋዮች በሙሉ በተዘረዘረው ግብር መክፈያ ፕሮግራም መሰረት በየግብር መክፈያ ተቋማችሁ በመቅረብ እንድትከፍሉ ስንል እያሳሰብን በየ ሩብ አመት እንደሚከተለው ቀ...
21/02/2026

ማስታወቂያ:-
ለአሶሳ ከተማ ግብር ከፋዮች በሙሉ በተዘረዘረው ግብር መክፈያ ፕሮግራም መሰረት በየግብር መክፈያ ተቋማችሁ በመቅረብ እንድትከፍሉ ስንል እያሳሰብን በየ ሩብ አመት እንደሚከተለው ቀርባዋል-
ከህዳር 1_30 /2018ዓ/ም=25%
ከየካቲት 1_30/2018/ዓም=25%
ከግንቦት 1_30/2018/ዓም=25%
ከሀምሌ 1_30/2018/ዓም=25% የመክፍል ግዴታ አለበት ዓመታዊ ግብሩን ያጠናቂቁ
የከቲት 13/2018ዓ/ም
" ገቢ ለልማት"
''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

Address

Asosa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asosa Town Administration Revenues Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share