05/04/2026
መጋቢት 24 ኢትዮጵያ ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው። የመላ ኢትዮጵያውያን ለውጥ የመሻት ፍላጎት ምላሽ ያገኘበት ዕለት ነው። የሁሉም ዜጋ ሕብረት የታየበት፤ ትብብርና አንድነት የተረጋገጠበት ዕለት ነው።
ለውጡ ኢትዮጵያዊያንን በሕብረት አስተባብሮ በጋራ አሻግሯል። ሀገርንም አጽንቷል። ለውጡ ትናንትን እያደሰ፣ ዛሬን እየለወጠ ጠንካራ ሀገር የመገንባት ሕልሙንና ትልሙን በተግባር እውን በማደረግ ቀጥሏል።
ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት የሀገር እና የሕዝብን ክብር ከፍ የሚያደርጉ ተጨባጭ ስኬቶች ተመዝግበዋል። የተጀመሩ ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የሀገራችንን ከፍታ የሚያረጋግጡ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አብስሯል። በሁሉም የልማት ዘርፎች አመርቂ ውጤት ተገኝቷል።
ሀገራዊ ለውጡ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ተግባራዊ በማድረግ የሀገራችን የፖለቲካ አውድና ባሕል ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እድል ፈጥሯል። ለውጡ ፈተናዎችን ወደ እድል የቀየረ፣ ወረትን ያዳበረ፣ የሀገራችን የቆየ አይበገሬነት ታሪክ ያረጋገጠ ሆኗል።
ከጠብመንጃ ይልቅ ምክክር እና ወይይትን፣ ከኃይል አማራጭ ይልቅ የሐሳብ ብዝሃነትን በማስቀደም በሀገራዊ ጉዳይ ላይ በትብብር አብሮ የመቆም አዲስ እሳቤን ፈጥሯል።
በመጭው ዘመንም ሕብረ ብሔራዊ አንድነታችን ጠብቀን የጀመርነውን የሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ በጋራ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል።