05/06/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን ከኢትዮ ቴሌኮም ደ/ደ/ም/ሪ ሪጂን ከመጡ ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ
ግንቦት፣27/2018 ዓም ሣውላ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የዳኝነት አገልግሎትን ተደራሽ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ ለማድረግ ከኢትዮ ቴለኮም ደ/ደ/ም/ሪ ሪጂን ልዑካን እና በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ የBusiness Admnistration and Information system ስራ ክፍል ጋር ውይይት አካሂዷል።
የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቦጋለ ፈይሳ የተገልጋዩን ጊዜ፣ ጉልበት እና ገንዘብ በመቆጠብ ፍርድ ቤቶችን ከቀደመው አሠራር በማላቀቅና በዘመናዊ ተክኖሎጂ በማስተሳሰር የመረጃ አያያዝ ለማዘመንና ወረቀት አልባ ፍርድ ቤቶችን ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አውስተው፤ ዲጂታላይዜሽን ቅንጦት ሳይሆን ሰው ተኮር አገልግሎት በላቀ ደረጃ በማዘመን ማህበረሰቡን መድረስ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
በኢትዮ ቴሌኮም ደ/ደ/ም ሪጂን የድርጅት ደምበኞች ሥ/አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ሞላ በበኩላቸው ድርጅቱ ፍርድ ቤቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን በባለፉት ጊዜያት በጎረቤት ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችም ጋር ሰፊ ስራ እየሰራ የነበረና ከደ/ኢ/ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋርም ወደፊት በሚደረሰው ስምምነት አግባብ ጥራትን መሠረት ያደረገ ፍርድ ቤቶችን በቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ ኃላፊነቱን በብቃት እንደምወጣ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ የBusiness Admnistration and Information system የሥራ ክፍል ኃላፊ፣ መምህራንና ባለሙያዎች ጋርም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዌብሳይት ማልማት ሥራ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል።
በፍርድ ቤቶቹ የሚለማው ዌብሳይት ተገልጋዩ ህብረተሰብ የሚፈልገውን መረጃ በቀላሉ እና በማንኛውም ስፍራ ሆኖ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ይህ ትብብር የዳኝነት ሥርዓቱን ወደ ዲጂታል ለውጥ በማሸጋገር ፈጣን፣ ግልጽ እና ተደራሽ የፍትሕ አገልግሎት ለማረጋገጥ አስፈላጊ እርምጃ መሆኑም ተጠቅሷል።
በዉይይቱ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱና የድርጅቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
👇 Follow & Share us 🙏
የአረካ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት