Arbegona TVET College

Arbegona TVET College Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Arbegona TVET College, Government Official, Arbegona, Arbe Gona.

✔️Hagiirru OdooQajeelsha Hasidhanno 12kki Kifile GumulaanoraArbagoonu Tekiniketenna Ogimmate Qajeelshi Kolleeje 2017 M.D...
22/10/2025

✔️Hagiirru Odoo
Qajeelsha Hasidhanno 12kki Kifile Gumulaanora
Arbagoonu Tekiniketenna Ogimmate Qajeelshi Kolleeje 2017 M.Dirira 12kki UEE Kifile guddinno Rosaano Loosunna Dandoote Ministere Tekinikenna Ogimmate Kolleejera Wortinno Eote Safaraanchi garinni babbaxxitinno Ogimmanni Deerra 1 Kayise Deerra 4 geeshsha Qajeelsha aate Qixxaawo guddinnota Ayiirrinyunni Xawinseemmo
Qajeelsha adhate wonshinanni Safaraanchu
✔️ 8 kifilenni kayise 12 kifile geeshsha noo Transcript
✔️12 kifile UEE Guma
✔️Lame 3/4 Footo
Cost sharing Batooshshe 450 Birra Sidaamu Baankera 3407302000047 Eo assitine slipe amaddine Barra10/02/2018M.D kaysine borreessantinanni gede egensiinseemmo
ለበለጠ መረጃ:- 0964010099 ፣ 0926384183 እና 0916502918 ይደውሉ
የ አርቤጎና ቴ/ሙ/ሥ/ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም በሥራና ክህሎት ሚኒስትር የኮሌጅ መግቢያ መስፈርት መሰረት የ12 ክፍል አጠናቃቂዎችን ከደረጃ 1 እስከ 4 በቀን መደበኛ፣በማታ እና በሳምቱ መጨረሻ መደበኛ መርሃግብሮች ሠልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ማብቃት እንዲሁም ሥራ ፈጣሪ ማድረግ ይፈልጋል።
በመደበኛ ከደረጃ 1 - 4 የሥልጠና መስክ
✔️ Agro Processing 2-4
✔️በእንስሳት እርባታ (Animal production )1-4
✔️የኮምፕዩተር ሥልጠና (HNS)1-4
✔️ Mechanics 1-4
✔️Wood Work Technology 1-4
✔️Building Electrical Installation1-4
✔️Animal Health1-4
ለመደበኛ መመዝግቢያ መስፍረት
👉 ለደረጃ 3 እና 4
➡ ወንዶች 135 እና ከዚያ በላይ
➡ ሰቶች 122 እና ከዚያ በላይ
👉 ለደረጃ 1 እና 2
➡ለወንዶች 134 እና ከዚያ በላይ
➡ለሰቶች 121 እና ከዚያ በላይ
በአጭር ጊዜ ሥልጠና ብቻ የሚሰጡ ሙያዎች 👇
1ኛ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ (BBEI)
2ኛ, ኮብልስቶን ስልጠና
3ኛ, መሰረታዊ የብረት ብየዳ ሥልጠና
4ኛ, በመደራጀት በማንኛውም ሙያ መሰልጠን ለሚፈልጉ በመረጡት ሙያ መስመሮች የአጭር ጊዜ ሥልጠና እንሰጣለን።
ማሳሰቢያ :- ከላይ በተጠቀሱት በቀን መደበኛ ሥልጠና ለመሰልጠን የምትፈልጉ ሠልጣኞች የ8ኛ ክፍል እና የ12ኛ ክፍል ዶክመንታችሁን ኦሪጅናሉ እስክመጣ ዳውንሎድ በማድረግ ዶክመንት የመጣላችሁ ዋናውንና የማይመለስ 1ኮፕ በዶሴ ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ በማድረግ በኮሌጁ የውስጥ ገቢ አካውንት ሲዳማ ባንክ አካውንት ( 3407302000047 ) የወጭ መጋራት 450ብር ገቢ በማድረግ የባንክ ደረሰኝ በደማቁ ከባንክ በመቀበል በኮሌጁ ሬጅስትራር ቢሮ በመቅረብ ከቀን 10/02/2018 ዓ.ም ዕለት ሰኞ ጀምሮ በመምጣት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገለጽለን ።
ለበለጠ መረጃ:- 0964010099 ፣ 0926384183 እና 0916502918 ይደውሉ

+++EGENSIISHSHA+++++++======================++Arbegoonu Te/Og/Qa/Kolleeje 2018 Qajeelshu dirira hawalle keerunni iilliti...
11/09/2025

+++EGENSIISHSHA+++
++++======================++
Arbegoonu Te/Og/Qa/Kolleeje 2018 Qajeelshu dirira hawalle keerunni iillitini yitanni, 2017 M.D babbaxitino ogimmanni qajeeltinanni galtinoonni qajeelaanonke baalantinni Qajeelsha hananfeemmo daafira barra wocawaaro 05, 2018 M.D kayse Wocawaaro 16, 2018 M.D geeshsha calla borreessinannihura yinoonni yannanni rahoteenni kollejete leeltine borreessamatenni qajeelsha adhitinanni gede duu'ne egensiinseemmo.

20/08/2025

"ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል"፦ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን

ነሀሴ 12/2017 የኢፌዴሪ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘመናት የገጠሟትን የኢኮኖሚ ስብራቶች ለመጠገንና ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ግስጋሤ ለማፋጠን አዲስ የኢኮኖሚ ልማት ዕይታ እና መንገድ እየተከተለች ትገኛለች። በተያዘው ብዝኃ ዘርፍ፣ ብዝኃ ተዋናይ እና ብዝኃ ተጠቃሚ የኢኮኖሚ ዕድገት አቅጣጫ፣ ለኢኮኖሚ ጥራትና አሳታፊነት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

እንደሚታወቀው፣ ሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን በመሠረታዊነት ለመፍታት ልዩ ልዩ ሪፎርሞችን ጀምራ እያሳካች ትገኛለች፡፡ የእነዚህ ሪፎርሞች ዓላማ ሁለት ነው፡፡

በአንድ በኩል ነባር ሀገራዊ ስብራቶችን መጠገንና የተንከባለሉ ዕዳዎችን ማቃለል ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የዛሬንና የነገን ትውልድ ጥያቄዎች በመመለስ፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና በአስተማማኝ መሠረት ላይ መገንባት ነው፡፡

ሪፎርሙን በመተግበር በተገኙ ውጤቶችና ትሩፋቶች፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች፣ የቢዝነስ አንቀሳቃሾችና በግል ክፍለ ኢኮኖሚ የተሠማሩ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የገቢ ሁኔታ ከኢኮኖሚ ዕድገቱ ጋር እየጨመረ መጥቷል፡፡ ነገር ግን የቋሚ ደመወዝተኞች በተለይም የመንግሥት ሠራተኞች ገቢ በተገቢው መጠን ሊጨምር አልቻለም፡፡

በአንድ በኩል በየጊዜው እየጨመረ በመጣው ሰፊ የመንግሥት ሠራተኛ ቁጥር ምክንያት የመንግሥት አጠቃላይ የደመወዝ ወጪ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት ለደመወዝ የሚያውለው ወጪ ከአጠቃላይ የመንግሥት ወጪ አንጻር ያለው ድርሻ ከ30 እስከ 32 በመቶ ይደርሳል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለእያንዳንዱ የመንግሥት ሠራተኛ የሚከፈለው ደመወዝ በሚፈለገው መልክ መጨመር ባለመቻሉ አሁንም የሚከፈለው አነስተኛ ነው፡፡

ይሄንን በመረዳት እና በየጊዜው በመንግሥት ሠራተኛው በተለይም ዝቅተኛ ተከፋይ በሆነው ላይ እየደረሰ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል፣ በ2017 በጀት ዓመት 91 ቢሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ እንዲሻሻል ተደርጓል። ያለፈው የበጀት ዓመት እንደ ሀገር ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የገባንበትና በመንግሥት ወጪ ላይ ከፍተኛ ጫና የነበረበት ዓመት ቢሆንም፣ መንግሥት ባለው ቁርጠኛ ሰው ተኮር አቋም፣ የዝቅተኛ ተከፋይ ሠራተኛውን ደመወዝ ትርጉም ባለው ሁኔታ አሻሽሏል።

ደመወዝ ከመጨመር ባለፈ ቋሚ ገቢ ያለውን ሠራተኛ የመግዛት ዐቅም ለማሳደግ፣ መንግሥት ከ1994 ዓም ጀምሮ ሥራ ላይ በቆየው የቁርጥ ገቢ ግብር ዐዋጅ ውስጥ በተካተቱት የግብር ማስከፈያ ምጣኔ እና በተለያየ ደረጃ ግብር በሚጣልበት የገቢ ቅንፍ(income bracket) ላይ ማስተካከያ አድርጓል፡፡ በዚህም ሰፊ ማሻሻያ የተደረገ ሲሆን፣ በተለይም ከታክስ ነጻ የሆነውን የተቀጣሪ ገቢ ከብር 600 ወደ ብር 2000 ለማሳደግ ተችሏል።

መንግሥት ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን የመንግሥት ሠራተኛ ዝቅተኛ የክፍያ ሁኔታ እና ተያይዞ የመጣውን የኑሮ ጫና በአንድ ጊዜ በሚደረግ የደመወዝ ማሻሻያ ሊቀርፈው እንደማይችል ይገነዘባል። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መንግሥት ከእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብልጽግና ምዕራፍ ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ መሆን አለበት ብሎ ደግሞ ያምናል። ስለሆነም ከሚወሰዱ ሌሎች ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

በዚህ ማሻሻያ፦

1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

2. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

3. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11,500 ይሻሻላል።

4. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል፡፡ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል። ይህ የደመወዝ ጭማሪ ካለን የልማት ፍላጎት አንጻር አገልግሎቶችና መሠረተ ልማት ለማስፋፋት የሚያስፈልገንን ሀብት የሚሻማ ቢሆንም፣ የመንግሥት ሠራተኛውን ኑሮ ማሻሻል ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ የተወሰነ ነው። ከዚህም ባሻገር የመንግሥት ሠራተኛው ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድን ሽፋንን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎች ይወሰዳሉ፡፡

መንግሥት ይሄንን የደመወዝ ማሻሻያ ሲያደርግ ጭማሪው በቂና የመጨረሻ ነው ብሎ በማመን አይደለም፡፡ በቀጣይነት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ማሻሻያው እየተተገበረ ሲሄድ ውጤትን መሠረት ያደረጉ ማሻሻያዎች ይደረጋሉ፡፡ በተጨማሪም የጀመርነው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ይበልጥ ውጤት እያስመዘገበ በሄደ ቁጥር፣ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የትሩፋቱ ተቋዳሽ ይሆናል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም በተገቢ ደረጃና መጠን ለመክፈል ከተፈለገ፣ ያንን የሚሸከም ሀገራዊ ኢኮኖሚ መገንባት አለብን፡፡

ኢትዮጵያ ለአገልጋዮቿ ተገቢውን ክፍያ እንድትከፍል የሚያስችላትን ኢኮኖሚ የመገንባት ኃላፊነት ደግሞ፣ በመንግሥት ሠራተኛው ላይ ጭምር የተጣለ ብሔራዊ ግዴታ ነው፡፡ ካልተከልነው ዛፍ ፍሬ፣ ካልዘራነው ሰብል ምርት ልናገኝ አንችልምና፡፡

ኢኮኖሚያችን ካላደገ፣ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ሊያድግ አይችልም፡፡ ለአብነት የታክስ ገቢያችንን በአንድ በመቶ ብናሳድግ እንኳን፣ ከ3ዐዐ ቢሊዮን በላይ ተጨማሪ ሀገራዊ ገቢ እናገኛለን፡፡ ይሄንን ለማሳካት ደግሞ በየመስኩ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ከፍተኛውን ሚና ይጫወታሉ፡፡

በአጠቃላይ ዘላቂና ትርጉም ያለው የኑሮ ደረጃ መሻሻል እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዓይናችንን ለአፍታም ቢሆን ከሀገራዊ ሕልማችን ሳንነቅል መረባረብ አለብን። በዚህ ሂደት ውስጥ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉት የውዴታ መሥዋዕትነት አለ፡፡ ይህ መሥዋዕትነት ለነገ ሲባል የሚከፈል መሥዋዕትነት ነው፡፡ ለተሻለ ነገ ስንል የተወሰኑ ፍላጎቶቻችንን እንተዋለን፡፡

ውድ ዕውቀታችንን፣ ጊዜያችንን እና ጉልበታችንን እንሠዋለን፡፡ ያደጉ ሀገራት ሁሉ የከፍታ ማማ ላይ የደረሱት በአንድ ወቅት መሥዋዕትነት በከፈሉ ትውልዶቻቸው ትከሻ ላይ ነው፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን በነጻነት የምንኖረው፣ ከመኖር ለሚበልጥ ሀገራዊና ሕዝባዊ ክብር ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን በሠው ዐርበኞቻችን ምክንያት ነው፡፡ የኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች የድካማቸውን ያህል ክፍያ እንደማያገኙ ይታወቃል፡፡

ይሄም ለተሻለች ኢትዮጵያ እየተከፈለ ያለ መሥዋዕትነት እንደሆነ መንግሥት ዕውቅና ይሰጣል። ስለሆነም በዚሁ አጋጣሚ፣ በአነስተኛ ክፍያ ሕዝብና መንግሥት የሰጣቸውን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ለሚገኙ አገልጋዮች መንግሥት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

በመጨረሻም ሕዝባችንን በንጽሕናና በትጋት በማገልገል፤ ከሚገባንና ከሚጠበቅብን በላይ በመሥራት፤ ሙስናና ብልሹ አሠራርን በመታገል፤ ከዕቅዶቻችን በላይ በማከናወን፤ የኢትዮጵያን ብልጽግና እንደምናረጋግጥ መንግሥት ጽኑ እምነት አለው፡፡

የብልጽግና ጉዟችን በቀጠለ መጠን፣ በየምዕራፉ ሁላችንም የብልጽግናን ትሩፋት መቋደሳችን አይቀሬ ነው፡፡ ለዚያ ደግሞ ሁላችንም ወገባችንን አጥብቀንና ታጥቀን መትጋት አለብን፡፡ ይህ ሲሳካ ነጻነታችንን በደማቸው እንዳጎናጸፉን ቀደምት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ሁሉ፣ እኛም ሀገራቸውን ለማበልጸግ ዋጋ የከፈሉ ትውልዶች ተብለን ታሪክ ሲዘክረን ይኖራል ስል። ዘገባው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ነው።

©የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ

20/08/2025

2018 ከተስፋ ወደሚጨበጥ ብርሃን!

ፓርቲያችን የሀገርን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚረጋገጠው የዜጎችን መሰረታዊ ጥያቄዎችን በተሟላ አኳሃን ተቋማዊ ሪፎርሞችን በማከናወን መመለስ ሲቻል መሆኑን ያምናል።

በዚህም ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

prosperity

05/05/2025
19/04/2025
28/03/2025

ለመላው ህዝባችን እንኳን የሲዳማ ህዝብ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሠላም አደረሳችሁ/አደረሰን ስል የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ መልዕክቱን ያስተላልፋል ።

ፊቼ ጫምባላላ በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ ከአሮጌው አመት ወደ አድስ አመት የሚሸጋገርበት ዘመን መለወጫና ማብሰሪያ ሆኖ የሚከበር ታላቅ በዓል ነው።

ከተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የማይዳሰሱ ቅርሶች መካከል ከተመዘገበ እንሆ 10 አመት አስቆጥሯል።

ፊቼ ጫምባላላ የዘመን መለወጫ በዓል ከሀገር ሀብቶችና ቅርሶች መካከል አንዱ በሆን ይህ በዓል በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣ ባህላዊ ትውፊት ነው፡፡

ፊቼ ጫምባላላ የአብሮነት፣ የሰላም፣ የፍቅርና የመረዳዳት እሴቶች ጎልቶ የሚታዩበት በዓል ነው፡፡

በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ዘመን መለወጫ በዓል ብቻም ሳይሆን ከዚህ በፊት የነበረ ቂምና ቁርሾ ተወግዶ ይቅርታ የሚሰፍንበት የእርቅና የሰላም ባህላዊ ትውፊት ነው። በመሆኑም ፊቼ ጫምባላላ የሰላም፣ የእርቅና የይቅርታ ተምሳሌት የሆነ ቅርሳችን ነው፡፡

በዓሉ የሠላም ፣ የፍቅር ፣ የእርቅ ፣ የመቻቻልና የመረዳዳት የአብሮነት እንድሁም የብልጽግና እንዲሆንልን እንመኛለን።

ፊቼ ጄጂ!!
የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ

28/03/2025

Wo'ma dagankera hawalle Sidaamu daga diru soorro fichee_cambalaallate ayyaana keerunni iillishi'ne/iillishinke!

Fichee_cambalaalla Sidaamu daga akkalu dirinni haaru dirira sa'nanni diru soorrora ayirinsanni bayra ayyaanaati.

Halantino mangistuwa uurrinshanni rosu, sayinsetenna budu(UNESCO) amandannikki dona assite maareekkitunkunni kune tonne dirra kiirantino.

Fichee_cambalaalla diru soorro ayyaani gobbate jironna doni giddo mitte ikkite, daga widoonni bayra baycho uynannitenna ilamatenni ilama sa'anni dagginote.

Fichee_cambalaalla baxillu, mittimma, keerunna ledama giddose amaddino.

Ayyaanu Sidaamu daga diru soorroha calla ikkikkinni, konni albaanni noo morkanna huluullo agurre araaranna keere dudumbanni keeru ayyaanaati.

Ayyaanu keerunniha, baxillunniha, mittimmanniha hattono jireenyunniha ikkara biiro halchose xawissanno.

Fichee_Jeeji!!

Sidaamu Qoqqowi Loosu Dandootenna lnterprayzootu Latishshi Biiro.

Address

Arbegona
Arbe Gona

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbegona TVET College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share