11/04/2026
የትንሳኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ የህግ ታራሚዎች በይቅርታ ተፈቱ።
ጨንቻ ቀን 03/08/2018 ዓ/ም። //የተቋሙ ህዝብ ግንኙነት//
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የ2018 ዓ/ም በጄት አመት የትንሳኤ በዓል ምክኒያት በማድረግ 3ኛ ዙር በይቅርታ እንዲፈቱ ከተወሰነላቸው የህግ ታራሚዎች መካከል ከጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ሙሉ ይቅርታ የተደረገላቸው ወንድ 39 ሴት -- ጠ/ድ 39 መሆናቸውን የተቋሙ አዛዥ ም/ኮሚሽነር አጥናፉ አሰፋ ገልፀዋል።
የጨንቻ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ ለህግ ታራሚዎች ከማህበረሰቡ ጋር በሚቀላቀሉበት ወቅት በማረሚያ ተቋም ቆይታ ጊዜ የተማሩትን ትምህርት በተግባር ማሳየት ይገባቸዋል ወንጀል አስከፊ መሆኑን መኮነን ይገባቸዋል በማለት የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰተዋል።
የጨንቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ተወካይ ረ/ኢ/ር ሙሉቀን ያጌ ወንጀል አስከፊ መሆኑን በመጥቀስ ዛሬ የተፈታችሁ ከማህበረሰቡ ጋር ዕርቅ በመፈፀም በሰላም ልትኖሩ ይገባል በማረሚያ ቆይታችሁ የተማራችሁትን ወደ ተግባር የምትቀይሩበት ጊዜ በመሆኑ ወንጄልን ለመከላከል አንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ በማለት አሳስበዋል።
ጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለለውጥ እንተጋለን።