የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ/ Gamo Zone Justice Department

የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ/ Gamo Zone Justice Department ይህ የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ሲሆን፣ በዚህ ገጽ የመምሪያዉ መልክት እና ወቅታዊ መረጃዎች ይተላለፋሉ።

17/04/2025
17/04/2025

የፋስካ በዓልን ምክንንያት በማድረግ 249 የህግ ታራሚዎች ከአ/ምንጭ እና ጨንቻ ማረሚያ ተቋማት በይቀርታ እንዲቀላቀሉ ተደረገ፡፡

አርባምንጭ: ሚያዝያ 9/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን መንግስ ኮሚዩኒኬሽን )፦የወንጀል ፍትህ ፖሊሲ መሰረታዊ አላማው ወንጀልን መከላከል ተፈጽሞም ሲገኝም በተገቢዉ መንገድ የሕግ ተጠያቂነትን ማስፍን እንደመሆኑ በዚህ ሂደት ወስጥ ወደ ወንጀል የፈፀሙ ዜጎችን አርሞና አንፆ በመልካም ስነ ምግባር ወደ ማህበረሰቡ ማቀላቀል መሰረታዊ የፖሊሲዉ ምሰሶ መሆኑን የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጤናሁን ጨርቆስ ገልጿል ።

እንደኅላፊው ገለፃ የፖሊስ እና የህግ ማዕቀፍ መሰረት በማደረግ የዞኑ የይቅርታ ምልመላና መረጣ ኮሚቴ በዞኑ ባሉ ሁለቱም ማረሚያ ተቋማት በአመት ሁለት ዙር የእስር ጊዜያቸዉ ለይቅርታ የደረሱ ታራሚዎችን በልዩ እና በመደበኛ ይቅርታ ማዕቀፎች ተጠቃሚ ሲያደርግ መቆየቱንም ተናግረዋ።

በዚህም የዘንደሮን አዲስ አመት በማስመልከት የመጀመሪያ ዙር የይቅርታ ስራ ተሰርቶ ከ200 በላይ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ተቀላቅለዉ በጎ አስተዋጽኦ በህበረተሰቡ ዘንድ እያበረከቱ የሚገኙ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ለሁለተኛ ዙር የእስር ጊዜያቸዉ ለይቅርታ የደረሱ 249 ታራሚዎችን የዞኑ የይቅርታ ምልመላና መርጣ ኮሚቴ አጣርቶ ለክልሉ የይቅርታ ቦርድ ያቀረበ ሲሆን ቦርዱም ተገቢዉን ማጣራት በማደረግ ይቀርታዉን የሰጠ በመሆኑም አመላክተዋል።

በዛሬዉ እለት ይቅርታ የተደረገላቸዉ ታራሚዎች ወደ ሕብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ መደረጉንና በዚህ ዙር የይቅርታ ስራ በተለየ መልኩ ማረሚያ ተቋማት ዉስጥ ያሉ ሴቶችን፣ በእደሜ የገፉ ታረሚዎችን ተጠቃሚ ማደረግ የተቻለ ሲሆን በዚህም ከአጠቃላዩ የይቅርታ ተጠቃሚዎች 21 ሴቶች፣ 5 ከህጻናት ጋር ያሉ እናቶች እንዲሁም 4 በእደሜ የገፉ ታራሚዎች እንዲለቀቁ ተደርጓል፡፡

አክለውም ታራሚዎችም ወደ ሕብረተሱ ሲቀላቀሉ መንግሰት የሰጣቸዉን እድል በመጠቀም በሚኖሩበት ማህበረሰብ ዉስጥ መልካም አርአያ እንዲሆኑና ማህበረሰቡንም እንዲኪሱ፣ እንዲሁም የሚቀበላቸዉም ማህበረሰብም በይቅርታ የወጡ ታራሚዎች ታረመዉና ታንፀዉ የወጡ መሆኑን በመረዳት በሁለንተናዊ ማህብረስብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ዉስጥ ማሳተፍና አቅማቸዉንም ለልማት መጠቀም እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

03/04/2025

በክልሉ የፍትህ ትራንስፎርሜሽን አፈጻጸም እንዲሳለጥ የሚደረገው ጥረት የሚበረታታ መሆኑ ተገለፀ

መጋቢት 25/2017 ዓ.ም

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍርድ ቤቶች የለውጥ ፍኖተ ካርታ እና የፍትህ ተቋማት ትራንስፎርሜሽን ዙሪያ በአርባ ምንጭ ከተማ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ በ6 ወር በፍርድ ቤቶች እና በፍትህ ተቋማት እንዲሁም የሶስትዮሽ ግንኙነት በማጠናከር ረገድና ህብረተሰቡ ወንጀል በመፀየፍ ሰላም ወዳድ እንዲሆን የሀገር በቀል የግጭት አፈታት ስርዓቶችን ተጠቅመው ግጭቶችን በመፍታት ወንጀል እንዲቀነስ የተሰራበት መንገድ አበረታች መሆኑ ተገልጿል።

በቀጣይ ማረሚያ ቤቶች አከባቢ አልፎ አልፎ የታራሚዎች አያያዝ፣የምግብ አቅርቦ ጥራት፣ የሴቶች መብት አያያዝ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የፍትህ አካላት ወርዶ ማየትና መፈተሽ በቀጣይ በትኩረት ሊሰሩ የሚገቡ ጉዳዮች መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ በኢፌዲሪ የህግና፣ፍትህ አስተዳደር ዘርፍ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የተከበሩ ወ/ሮ ፋናዬ መለሰ ናቸው።

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ ፍትህና አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት የተከበሩ አቶ ወጌ ቁፋ ፍርድ ቤቶችና ፍትህ ተቋማት ቴክኖሎጂ በማዘመን ቀልጣፋና ፈጣን የውሳኔ አሰጣጥን ማሳደግና ተቋማዊ አደረጃጀትን ማጠናከር ከፍትህ ተቋማት የሚጠብቁ ውጤቶች መሆናቸውን አንስተዋል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብነዘር ተረፈ የህብረተሰቡን የፍትህ ተደራሽነትና ፈጣን አገልግሎትን በማሳደግ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቋሙ ይሰራል ብለዋል።

አክለውም ተቋሙን በቴክኖሎጂ በማዘመን ለአገልግሎት ምቹና ማራክ የማድረግ ሥራዎችን፣ቅንጅታዊ አሰራሮች፣የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣የሴቶች መብት ከለላ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት የሚሰሩ ሥራዎች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አንስተዋል።

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕረዚዳንት የተከበሩ አቶ አንዷለም አምባዬ በበኩላቸው በፍርድ ቤቶች አኳያ ከመደበኛው ህግ ውጪ በየጊዜው እየተስፋፋ የሚመጡ ወንጀሎች ህብረተሰቡ በባህላዊ ህግ አሰራር ችግሮች እየተፈቱ እንድሄዱ በመግለፅ በቀጣይም ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ አንስተዋል።

እንደ ምክትል ፕረዚዳንቱ ገለጻ ፍርድ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ ለማዘመን እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው ከመደበኛ በጀት ውጪ ተጨማሪ በጀቶች እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

ክልሉ አዲስ ክልል ከመሆኑ አንፃር የፌደራል ፍርድ ቤቶችና ፍትህ ተቋማት ድጋፍን በእጅጉ እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።

በሀገር ደርጃ የተጀመረውን የፍትህ ተቋማት ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች በክልሉ ተጨባጭ ሁኔታ በፍርድ ቤቶችና በፍትህ ተቋማት ላይ የሪፎርም ተግባራት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተናገሩት ደግሞ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ናቸው።

አፈ-ጉባኤው አሁን የተጀመሩ የፍትህ ትራንስፎርሜሽን የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው እንድቀጥሉ ማድረግ፣ማረሚያ ተቋማት አከባቢ የተጀመሩ የተቋማት ግንባታ ሥራዎች ትኩረት እንደሚሰጥና በስትሪንግ ኮሚቴ በመገምገም ውሳኔዎችን ማሳለፍ ከኮሚቴ የሚጠበቁ ተግባራት መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ቡድኑ በክልሉ ቆይታ በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ፍትህ መምሪያ እና የጨንቻ ከተማ ማረሚያ ቤት ተዘዋውረው እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።

31/03/2025
30/03/2025
የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የንብረት ማስመለስ  አዋጅ ቁጥር 1364/2017ን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ****************የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስ...
30/03/2025

የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017ን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ
****************
የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ጥር 1ቀን 2017 ዓ.ም የፀደቀዉን የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017ን አስመልክቶ ለመንግስት እና የግል የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች በዛሬዉ እለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017 በጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን ተከትሎ የአዋጁን ዓላማ፣ መሠረታዊ ይዘቶች፣ እንዲሁም ቀጣይ አተገባበር በተመለከተ የተፈጠሩ ብዥታዎችን ለማጥራት መግለጫ መስጠት ማሰፈለጉን የገለፁት ክብርት ሚኒስትሯ፣ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በወንጀል የተገኘ ሃብት ማስመለስን በተመለከተ ራሱን የቻለና ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በሕግ ማስከበር ሂደት በጣም ክፍተት ፈጥሯል። የወንጀል ሕጉን ጨምሮ በተለያዩ አዋጆች የሃብት ማስመለስ ሥነ-ሥርዓትን በሚመለከት የተካተቱ ድንጋጌዎች በራሳቸው የተሟሉ ካለመሆናቸው ባለፈ አንዱን ከሌላው ጋር እያስማሙ ለመተግበር አስቸጋሪ የሚያደርጓቸው ድንጋጌዎችን የያዙ እና ተፈጻሚነታቸውም ውስን የሆኑ ወንጀሎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተቀረጹ በመሆኑ በርካታ በማህበረሰቡ ላይ ጉዳትን በሚያደርሱ ወንጀሎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ አልተቻልም። በዚህም ወንጀል ፈፃሚዎች ከወንጀል ድርጊት ያገኙትን ንብረቶች በማስመለስ ረገድ ከፍተኛ የሆነ የሕግ እና አሰራር ክፈተቶች እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል።

ክብርት ሚኒስትሯ አክለውም ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ እስካሁን ባሉን ሕጎች ተጠያቂ የሚሆኑት የመንግሥትና ሕዝባዊ ድርጅት ሠራተኞች ሲሆኑ ሌሎች ሰዎችን የማይመለከት በመሆኑ ሰፊ በሚባል ደረጃ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት የማፍራት ሁኔታ ተስተውሏል። የዚህ ሕግ አለመኖር ሌሎች የመንግስትና ሕዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች በቀላሉ በሕገ-ወጥ መልኩ ያፈሩትን ንብረት በእነዚህ ሰዎች ስም ለማፍራት እና ለመደበቅ እንዲችሉ ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል ብለዋል።

በሌላ በኩል አዋጁ የዜጎችን የንብረት መብት ተገቢ ጥበቃ ለማረጋገጥ ብዙ ድንጋጌዎችን ያካተተ ነው ያሉት ክብርት ሚኒስትሯ፣ በቅን ልቦና ንብረትን የያዙ ሰዎች በቅን ልቦና የያዙት ንብረት እንዳይወረስ ተገቢውን ጥበቃ ሰጥቷል። ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በሚመለከት ለማስረዳት የሚቀርበው የማስረጃ አይነት እንደየአግባቡ የተለያየ ሊሆን ይችላል። የንብረቱን አመጣጥ የማስረዳት ሸክም ያለበት ሰው በማንኛውም ያስረዱልኛል በሚላቸው የማስረጃ አይነቶች ሊያስረዳ የሚችል ሲሆን የማስረጃው አጥጋቢነት ደግሞ በፍርድ ቤት የሚመዘን ይሆናል። በመሆኑም የንብረት ማስመለስ ሕግ መውጣት ዜጎች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖራቸውን የእኩል ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት እና የግለሰቦችን በሕጋዊ መንገድ ብቻ ንብረት የማፍራት ባህልን በማሳደግ ጠንካራ የሆነ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋዕፆ እንደሚኖረው አመላክተዋል።

የዚህ ሕግ አተገባበር በሰዎች የንብረት መብት ላይ ያልተገባ ተጽዕኖን እንዳይፈጥር እና የሕግ አስፈጻሚ አካላት ባልተገባ አሰራር የዜጎችን መብት እንዳይጥሱ በሚያስችል መልኩ እንዲተገበር አዋጁ የአደረጃጀት እና የአሰራር መፍትሔዎችን አካቷል ያሉት ክብርት ሚኒስተሯ፣ አዋጁ የሚተገበረው በፍትሕ ሚኒስቴር በተማከለ አደረጃጀት ለዚህ ሥራ ዓላማ በሚደራጅ የሥራ ክፍል በመሆኑ ግልጽ የአሠራር ሂደትና የተጠያቂነት ሥርዓት እንደሚዘረጋ ተገልፆል።

ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ በቅድመ ክስ ሂደት ማንኛውም ሰው ጉዳዩን እንዲያስረዳ የሚቀርቡ ጥያቄዎች እና አቤቱታዎች የፍርድ ቤቶች የሥነ ሥርዓት ሕጎችንና መርሆዎችን ተከትለው ጥብቅ የሆነ ማጣራት የሚደረግባቸው ሲሆን አቤቱታ የሚቀርብባቸውም ሰዎች በሕጉ መሰረት ያላቸውን ማስረጃዎች የማቅረብ እና በፍርድ ቤት ዘንድ ቀርበው የመደመጥ መብታቸው እንዲከበርላቸው ይደረጋል። ለሥራ ክፍሉ የሚቀርቡ ምንጩ ያልታወቀ ሀብትን የሚመለከቱ ጥቆማዎችም ሆነ ጥርጣሬዎች ጥብቅ በሆነ አሰራር የሚጣሩ እና በቂ ምክንያት መኖሩ የሚታመንባቸው ጉዳዮች ብቻ ወደ ፍርድ ቤት የሚሄዱበት የአሰራር ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናልም ተብሏል።

በአጠቃላይ የንብረት ማስመለስ ሕግ በኢትዮጵያ ሰዎች ከወንጀል ድርጊት የሚያፈሩትን ሀብት እና ምንጩ ሳይታወቅ የሚያገኙትን ንብረት በመቆጣጠር እና ሲገኝም ለማሕበረሰቡ ተመላሽ እንዲሆን በማድረግ ወንጀል አትራፊ ሥራ እንዳይሆን ማድረግን እና በአጠቃላይ ደግሞ ማህበራዊ ፍትሕን ማስፈንን አላማው አድርጎ የጸደቀ እና ይህንን ዓላማ በሚያሳካ አግባብ ጥብቅ የሆነ የአፈጻጸም ሥርዓትን የሚከተል የሕግ ማዕቀፍ ነው ሲሉ ክብርት ሚኒስተሯ አብራርተዋል።

የፍትህ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ

30/03/2025

the quality of being just; righteousness, equitableness, or moral rightness: to uphold the justice of a cause. rightfulness or lawfulness, as of a claim or title; justness of ground or reason: to complain with justice.

Address

አርባምጭ ቤሬ ቀበሌ
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ/ Gamo Zone Justice Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share