የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department ይህ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ እውቅና የተከፈተ ሕጋዊ የፌስ ቡክ ገጽ ነው። ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ም ተከፈተ

23/05/2026

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ስለ ውቢቷ አርባ ምንጭ ከተናገሩት
የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department
📷ከማህበራዊ ሚዲያ

23/05/2026

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department
📷ከማህበራዊ ሚዲያ

22/05/2026

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department
📷ከማህበራዊ ሚዲያ

በአርባ ምንጭ ከተማ በጫሞ ሃይቅ ሙላት ምክንያት የተነሱ በጋታ ቦቼ እና ላሜ ቀጠና የሰፈሩ ባለ ይዞታዎች የሳይት ፕላን ሰርቶ ለማስረከብ ሁለተኛ ዙር የተጀመረው የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ ...
17/05/2026

በአርባ ምንጭ ከተማ በጫሞ ሃይቅ ሙላት ምክንያት የተነሱ በጋታ ቦቼ እና ላሜ ቀጠና የሰፈሩ ባለ ይዞታዎች የሳይት ፕላን ሰርቶ ለማስረከብ ሁለተኛ ዙር የተጀመረው የማረጋገጥና የመመዝገብ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
‎ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

በአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር በሼቻ ክፍለ ከተማ በጋታ ቦቼና ላሜ ቀጠና በጫሞ ሃይቅ ሙላት ምክንያት ለተነሱ የሕብተሰብ ክፍሎች የቦታ ምዝገባና የማጣራት ሥራ በማጠናቀቅ፣ ለባለይዞታዎች የሳይት ፕላን ሰርቶ ለማስረከብ የተጀመረው ከፍተኛ ጥረት ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ መሸጋገሩ ተገለጸ።

የሕዝቡ የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየውን ይህንን ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት በከተማ አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በቁርጠኝነት እየተተገበረ ይገኛል። ለሥራው መሳካትም የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያና የክልል ባለሙያዎችን ያካተተ ጥምር የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ተግባር መግባቱ ታውቋል።

የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት መነሻ በማድረግ የአንደኛ ፌዝ (ምዕራፍ) ሥራዎችን በስኬት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የነዋሪውን ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ የቀበሌና የቀጠና አመራሮችን እንዲሁም የሀገር ሽማግለዎችን በንቃት በማሳተፍ የሁለተኛ ፌዝ ሥራዎችን በልዩ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ እንደገለጹት፣ ይህ የቦታ ማጣራትና የሳይት ፕላን ዝግጅት ሥራ የዜጎችን ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስና ፍትሃዊነትን ለማስፈን ታስቦ እየተከናወነ ያለ ወሳኝ ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለውም፣ ሂደቱ የተሳለጠና ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላትና የይዞታው ባለቤቶች በቦታው በአካል በመገኘት ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ለሥራው ውጤታማነትና ስኬትም እያንዳንዱ ባለይዞታ የበኩሉን አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ አቶ ደግፌ አማረ ጥብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ

➛Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61589064406953

➛Telegram
https://t.me/arbaminchcitylandadministration

➛Tiktok
tiktok.com/.minch.city.l

➛WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VbCk2LK2phHTvvVffP2W

➛E.mail
[email protected]

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ እውቅና የተቋቋመው ልዩ ቅሬታ ሰሚ ግብረ ኃይል በሻራ ቀበሌ የመስክ ምልከታ አካሄደ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖‎ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ...
15/05/2026

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ እውቅና የተቋቋመው ልዩ ቅሬታ ሰሚ ግብረ ኃይል በሻራ ቀበሌ የመስክ ምልከታ አካሄደ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
‎ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ እውቅና የተቋቋመው ልዩ ቅሬታ ሰሚ ግብረ ኃይል ቡድን ከመሬት ጋር የተያያዙ የህብረተሰብ ቅሬታዎችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ቀጥሏል። ግብረ ኃይሉ በዛሬው እለት ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በሻራ ቀበሌ አስተዳደር በመገኘት የመስክ ምልከታ አከናውኗል።

የግብረ ኃይሉ አባላት ቅሬታ አቅራቢ ባለጉዳዮችን በቦታው በማግኘት ያነጋገሩ ሲሆን፥ የቅሬታ መነሻ የሆኑትን ይዞታዎችና ተያያዥ ጉዳዮችን በአካል በመገኘት ዝርዝር ምልከታ ማድረጋቸው ታውቋል። ይህ የእለት ከእለት የመስክ ክትትል የህዝብን ቅሬታ በቦታው ላይ በመገኘትና ትክክለኛውን መረጃ መነሻ በማድረግ ምላሽ ለመስጠት የታለመ መሆኑ ተገልጿል።

ልዩ ግብረ ኃይሉ ቀደም ሲል በቦላ ጉርባ በተመሳሳይ መልኩ የመስክ ምልከታ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን፥ በወቅቱም ያጋጠሙ ችግሮችን በዝርዝር በመመዝገብና ወደ ቦታው ድረስ በመውረድ የችግሮቹን መነሻና ምንጭ በጥልቀት ሲመረምር መቆየቱ ተመላክቷል።

ቡድኑ በቀጣይም በሻራ ቀበሌም ሆነ በቦላ ጉርባ የተመዘገቡ ቅሬታዎችንና የተሰበሰቡ መረጃዎችን በጥልቀት በመመርመር፥ አሉታዊና አዎንታዊ የሆኑ ጉዳዮችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ሚዛናዊ በሆነ መንገድ እንደሚያጠና አስታውቋል። ግብረ ኃይሉ ይህንን ምርመራ ካጠናቀቀ በኋላ ዝርዝር ሪፖርትና የውሳኔ ሃሣብ ለመምሪያ ኃላፊ እና ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ምላሽ የሚሰጥ ይሆናል።

ይህ የመሬት አስተዳደር መምሪያው ልዩ ቅሬታ ሰሚ ግብረ ኃይል እያከናወነ የሚገኘው ተግባር፥ በከተማው የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ላይ የሚስተዋሉ የአሰራር ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም የነዋሪዎችን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በፍትሃዊነት ለመመለስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department
👇👇👇
➛Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61589064406953

➛Telegram
https://t.me/arbaminchcitylandadministration

➛Tiktok
tiktok.com/.minch.city.l

➛WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VbCk2LK2phHTvvVffP2W

➛E.mail
[email protected]

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር ዘርፍ የሚነሱ ቅሬታዎችን የሚፈታ ልዩ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገባ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት...
15/05/2026

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር ዘርፍ የሚነሱ ቅሬታዎችን የሚፈታ ልዩ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገባ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ፣ በተለያዩ ጊዜያት ሳይፈቱ የቆዩ ከመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል "ልዩ የቅሬታ ሰሚ ግብረ-ኃይል" አቋቁሞ ወደ ተግባር መግባቱን አስታወቀ።

ይህ ልዩ ግብረ-ኃይል የተቋቋመው በመምሪያው ኃላፊ በአቶ ደግፌ አማረ ቀጥተኛ መመሪያ ሰጭነት ሲሆን፣ ዓላማውም ከመደበኛው የቅሬታ ፈቺ አካል በተጨማሪ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ውስብስብ ቅሬታዎችንና ጥያቄዎችን አጣርቶ ምላሽ መስጠት ነው።

ልዩ ግብረ-ኃይሉ በዛሬው እለት በቦላ ጉርባ ቀበሌ አስተዳደር በአካል በመገኘት፣ ቅሬታ ካላቸው ባለጉዳዮች ጋር ለሦስተኛ ጊዜ የማጣራት ሥራዎችን አከናውኗል። ግብረ-ኃይሉ በቦታው ተገኝቶ መረጃዎችን በማሰባሰብና የቅሬታ አቅራቢዎችን አቤቱታ በመስማት የችግሮቹን ምንጭ የመለየት ሥራ ሰርቷል።

የልዩ ግብረ-ኃይሉ ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጮሎፎ እንደገለጹት፣ ግብረ-ኃይሉ አምስት አባላት ያሉት ሲሆን፣ በቀጣይም በሻራ ቀበሌ አስተዳደር በመውረድ ተመሳሳይ የማጣራት ተግባራትን ያከናውናል። ሰብሳቢው አክለውም የማጣራት ሥራው ቅሬታዎች በሚነሱባቸው በሁሉም የከተማዋ ክልል ውስጥ በሚገኙ ቀበሌያት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለሕዝብ ጥያቄዎች ተገቢው ምላሽ እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች መሬትና መሬት ነክ የሆኑ ጉዳዮችን በተመለከተ ቅሬታ ካላቸው፣ ጉዳዩን ከሙሉ መረጃና ማስረጃ ጋር በማያያዝ ለዚህ ልዩ ቅሬታ ሰሚ ግብረ-ኃይል በማመልከቻ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ አዲስ አሰራር በከተማዋ ያለውን የመሬት አስተዳደር አገልግሎት ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ እንዲሁም በመደበኛው የቅሬታ አፈታት ትኩረት ያላገኙና ለዓመታት የቆዩ የሕዝብ ቅሬታዎችን በፍትሃዊ መንገድ ለመፍታት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

@የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ
➛Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61589064406953

➛Telegram
https://t.me/arbaminchcitylandadministration

➛Tiktok
tiktok.com/.minch.city.l

➛WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VbCk2LK2phHTvvVffP2W

➛E.mail
[email protected]

14/05/2026

በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ውስጥ የሚሰሩ ባለሞያና የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊና አባል የሆኑ የመምሪያው ሰራተኞች በዛሬው እለት በአርባ ምንጭ ከተማ በተካሄደው ክልል አቀፍ የብልጽግና ፓርቲ ቅስቀሳ ላይ የነበረው ኩነት።

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚደረገው የቅስቀሳ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖‎ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ የአር...
14/05/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚደረገው የቅስቀሳ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
‎ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሀዊ እና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉ በተገለጸበት መድረክ፤ በአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የተሳተፉበት ሰፊ የምርጫ ቅስቀሳ ተካሄደ።

በዕለቱ በተከናወነው የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምስ አድማሱ የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ እንዲሁም በጋሞ ዞን የፓርቲው ዕጩ ተወዳዳሪዎችና በርካታ የፓርቲው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

ክልሉ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ በሁሉም ረገድ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁ ተገልጿል። በምርጫው የሚሳተፉ ፓርቲዎች በሕግ በተፈቀደው አግባብ ፕሮግራሞቻቸውንና ዕጩ ተወዳዳሪዎቻቸውን ለሕዝብ ሲያስተዋውቁ መቆየታቸው ተመላክቷል።

ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት አገር ለማሻገር የሰነቀውን ራዕይና የነደፋቸውን ፕሮግራሞች ለሕዝቡ በስፋት አቅርቧል።

በቅስቀሳ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት አመራሮችና ዕጩ ተወዳዳሪዎች ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸውን ውጤቶች በማስታወስ፤ በቀጣይም ለከተማዋና ለክልሉ ልማት፣ ሰላምና ብልጽግና የተያዙ ዕቅዶችን ለነዋሪው አብራርተዋል።

በተለይም የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ፣የመምሪያው የብልጽግና ፓርቲ የቤተሰብ ሰብሳቢና የሕብረት አመራር አቶ ኤርሚያስ ዶዳ፣ የመምሪያው ሠራተኞች የፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በነቃ ተሳትፎ የምርጫ ቅስቀሳውን በደመቀ ሁኔታ አከናውነዋል።

@የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ
➛Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61589064406953

➛Telegram
https://t.me/arbaminchcitylandadministration

➛Tiktok
tiktok.com/.minch.city.l

➛WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VbCk2LK2phHTvvVffP2W

➛E.mail
[email protected]

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ የማኔጅመንት አባላት በበየነ መረብ በወቅታዊ የምርጫ ሥራና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ውይይት አደረገ።➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖‎ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ...
13/05/2026

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ የማኔጅመንት አባላት በበየነ መረብ በወቅታዊ የምርጫ ሥራና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ውይይት አደረገ።
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
‎ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department

የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ከማነጅመንት አባላት ጋር በ2018 ዓ/ም ወቅታዊ የምርጫ ሥራ እና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ በበየነ መረብ (Online) ጠንካራ ውይይት አካሄደ።

ውይይቱን የመሩት የመሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ ሲሆኑ፣ በመድረኩም በመሬት አስተዳደር ዘርፍ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ተለይተው በፍጥነት ሊፈቱ በሚገቡባቸው ሁኔታዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በተለይም አገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ ኃላፊው አሳስበዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ2018 ዓ/ም የምርጫ ሥራ በስኬት እንዲጠናቀቅ መምሪያው ያለበትን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣና ለሥራው አስፈላጊው ዝግጅት እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደግፌ አማረ በቀጣይ ተግባራት ላይ ግልጽ መመሪያና የሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የዕለቱን የሥራ ውይይት አጠናቀዋል።

@የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ

➛Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61589064406953

➛Telegram
https://t.me/arbaminchcitylandadministration

➛Tiktok
tiktok.com/.minch.city.l

➛WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VbCk2LK2phHTvvVffP2W

➛E.mail
[email protected]

Address

Ethiopian
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአርባ ምንጭ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ Arba Minch City Land Administration Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share