Arbaminch Zuria Woreda Women & Children Affairs Office

Arbaminch  Zuria Woreda Women & Children Affairs Office This page is the media center of Arbaminch Zuria woreda Women and Social Affairs Office

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረዉ ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8)ቀንበድምቀት ተከበረ።በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ማህበ...
26/03/2026

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረዉ ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8)ቀን
በድምቀት ተከበረ።
በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በዓለም ለ115 ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን (ማርች ''የሴቶች ድምጽ እኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ቃል በድምቀት ተከብሯል።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን (ማርች ምክንያት በማድረግ በወረዳው በሚገኙ ቀበሌያት በተለያዩ ዝግጅቶች ስከበር መሰንበቱን ወ/ሮ ዝዋይ ደለለኝ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል።
የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ( ማርች 8 ) ታሪካዊ መነሻው የሠራተኞች እንቅስቃሴ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በተመድ ዕውቅና የተሰጠው ዓመታዊ ክብረ በዓል ለመሆን መብቃቱን ወ/ሮ ዝዋይ አስታውሰዋል።
በመሆኑም ሴቶች ከወንዶች እኩል የመስራት፣ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ፣ የመሰብሰብ እና የመምራት መብቶቻቸዉን ለማስከበር መደራጀትና በጋራ መስራት እንደሚገባ ወ/ሮ ዝዋይ ገልፀው ሴቶች ለራሳቸውም ይሁን ለሀገራቸው ለውጥና እድገት ተግተው መስራትም ይጠበቅባቸዋል ስሉ አሳስበዋል።
በመድረኩ የሴቶችን መብት ከማስከበር ባለፈ፣ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ሴቶች ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት በወሪት/ ቤተልሔም ይልማ የዕለቱ የክብር እንግዳ እና የወረዳው ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አማካኝነት ተላልፏል።
በመድረኩ ዕለቱን አስመልክቶ ስለማርች 8 የተዘጋጀ ሰነድ በአቶ መርጊያ ማንቻ የጽ/ቤቱ ሴቶች ንቅናቄና ተሳትፎ ማስፋፊያ ባለሙያ የቀረበ ሲሆን፤ ከህግ ማዕቀፍ ተጠቃሚነት እረገድ የተዘጋጀ ሰነድም በወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት አቃቤ ህግ በሆኑት በአቶ ጎሳ ጎጆ ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ በአርባምንጭ  ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በመገኘት የ1ኛ ሩብ ዓመት የክረምት ...
22/10/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ እና የጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በመገኘት የ1ኛ ሩብ ዓመት የክረምት በጎ ተግባር የተሰሩ ስራዎችን ድጋፍና ክትትል አደረጉ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በመገኘት የ1ኛ ሩብ ዓመት የክረምት በጎ ተግባር የተሰሩ ስራዎችን ድጋፍና ክትትል አድርገዋል።

የድጋፋዊ ክትትል ቡድኑን የመሩት የደቡብ ክልል የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህፃናት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ምህረት በላይ እንደተናገሩት በክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራትን በጥልቀት በማየት በጥንካሬ የተመዘገቡ ድሎችን በማስቀጠልና ደካማ አፈፃፀሞችን በመለየት በውጤት የታጀበ ስራ ለመስራት የሚያስችል ግምገማ መሆኑን ገልፀዋል።

‌‎የሴቶች ልማት ህብረት አደረጃጀቶች በማጠናከር ሴቶች በኢኮኖሚያዊ ፣ በፓለቲካዊና በማህበራዊው ዘርፍ በቅተው ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማስቻል ስራዎች በዝሁ በክረምት ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራት መሆኑን ገልፀዋል።

‎የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም የተሰሩ ስራዎች የአቅሜ ደካማና ለአረጋውያን የቤት እድሳትና ግንባታ፣ የደም ልገሳ፣ለችግር የተጋለጡ ሴቶችን የመደገፍ፣በሴቶች ልማት ህብረት የተሰሩ አቅም ለሌላቸው ድጋፍ መደረጉ ተገልጿል።

ህፃናት የሀገር ተረካቢነት ሚናን ይወጡ ዘንድ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።አርባምንጭ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም (የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) በአርባ ም...
28/06/2025

ህፃናት የሀገር ተረካቢነት ሚናን ይወጡ ዘንድ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

አርባምንጭ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም (የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት የህፃናት ፓርላማ 4ኛ ዙር 8ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል።

ህፃናት የሀገር ተረካቢነት ሚናን ይወጡ ዘንድ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ወ/ሮ ዝዋይ ደለለኝ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ለጉባኤው ተሳታፊዎች ባስተላለፉት የመክፈቻ ንግግር ተናግረዋል።

ወ/ሮ ዝዋይ አያይዘውም የህጻናት መብቶች ኮንቨንሽን በህገ መንግስት በተሰጣቸዉ የመደራጀት መብት በመጠቀም ተደራጅተዉ ተሳትፏቸዉንና ተጠቃሚነታቸዉን ማረጋገጥ እንዲችሉ ከተቋቋሙ አደረጃቶች አንዱ የህጻናት ፓርላማ ነዉ ብለዋል፡፡

የህጻናት ፓርላማ የህጻናት ተሳትፎ መብት የሚረጋገጥበት፣ ህጻናት መብቶች እንዲጠበቁ በተለያዩ ዘርፎች ተሳትፏቸዉ እንዲጎለብት ይረዳል ብለዋል ኃላፊዋ።

በጉባኤው ህፃን እሱባለው መብራቱ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የህፃናት ፓርላማ ዋና አፈ ጉባዔ አማካኝነት በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች የተከናወኑ ተግባራት በተለይም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ አፈፃፀም ሥራዎች ለምክር ቤት አባላቱ ቀርቧል።

በፓርላማው ዋና አፈጉባኤ በቀረበው የምክር ቤት ሪፖርት ዙሪያ አባላቱ ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎችን አቅርበዋል፣ በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ተገቢው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።

በጉባኤው ተሳተፊ አባላቱ ሥነ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ የምክር ቤቱ የቀጣይ ተግባራት አቅጣጫና ተልዕኮ በጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ዝዋይ ደለለኝ አማካኝነት ተቀምጦ ጉባኤው ተጠናቋል።

የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በአፍርካ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ34ኛ ጊዜ "የወደፊት ኢትዮጵያን በዛሬ ትውልድ እጅ ኃላፊነት አሁን ይጀምራል" በሚል መሪ ቃ...
20/06/2025

የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በአፍርካ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ34ኛ ጊዜ "የወደፊት ኢትዮጵያን በዛሬ ትውልድ እጅ ኃላፊነት አሁን ይጀምራል" በሚል መሪ ቃል የአፍርካ ህፃናት ቀን ማጠቃለያ መድረክ ተካህዷል፡፡
በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በሁሉም ትምህርት ቤቶች እየተካሄደ የቆየው የአፍርካ ህፃናት ቀን በዓል ማጠቃለያ መድረክ በወረዳ ደረጃ ከሁሉም ት/ት ቤቶች የተወጣጡ ተማሪዎችና የክበባት ተጠሪ መምህራን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተካህዷል፡፡
ወ/ሮ ዝዋይ ደለልከኝ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት ህፃናት መብታቸውንና ጥቅማቸውን አስከብረው እንድኖሩ መንግስት በህፃናት መብቶችና ጥበቃ ዙሪያ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ወረዳው በህፃናት መብቶችና ጥበቃ ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መቆየቱን የገለፁት ወ/ሮ ዝዋይ ነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ህፃናት በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ፣ የህፃናት ጉዳይ በመንግስትና በህብረተሰቡ ዘንድ ትኩረት እንድያገኝ፣ አለምአቀፋዊና አህጉራዊ የህፃናት መብቶችን ለማስከበር እንደሚሰራ አክለው አንስተዋል።
ለውይይት መነሻ ሰነድ የጽ/ቤቱ የህፃናት ስነልቦና ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ኩራባቸው ካቻራ አማካኝነት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
ህፃናት በህይወት የመኖር መብት፣ ወላጆችን ወይም በህግ የማደግ መብት ያላቸውን ሰዎች የማወቅ የእነርሱን እንክብካቤ የማግኘት መብት፣ ጉልበት ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ መብት፣ በትምህርት በጤናው በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎች እንዳይሰሩ መከላከል እንደሚችሉ አቶ ኩሪባቸው በሰነዱ መነሻ አንስተዋል።
የህፃናት መብቶች የተለያዩ መለያዎች ያሏቸው በህገመንግስትና በአዋጅ እንደተደነገገው ዓለምአቀፋዊና የማይገረሰሱ እንደሆኑና በህፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃትና ህገወጥ የህፃናት ዝውውርን ለማስቀረት የሚያስችል አሠራር ተዘርግቶ እየተሠራ እንደሚገኝ በመድረኩ ተብራርቷል።
ወረዳው ከዞኑ ጋር በመቀናጀት የህፃናትን መብትና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ እየሰራ ያለው ሥራ አበረታች እንደሆነ የጠቆሙት የውይይቱ ተሳታፊዎች በህፃናት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት በባህላዊ በሽምግልና ለመጨረስ የሚደረገው እንቅስቃሴ ልቆም ይገባል ብለዋል።
በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙና ድጋፍ የሚሹ ልጆች እንዲሁም ለሱስ ተጠቂ እየሆኑ ባሉ ህፃናት ዙሪያ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቀጣይ አቅደው ልሰሩ እንደሚገባም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመድረኩ የጽ/ቤቱ ማነጅመንት አካላት፣ የሁሉም ትምህርት ቤቶች የህፃናት ፓርላማ ክበብ ተጠሪ ተማሪዎችና መምህራን ተገኝተዋል።

Kawonne dereteththa qaaxon oothettishe diza gita dichcha oothota tamaare nayti yuuyi xeellana mala oothoy dic'c'iza gada...
06/06/2025

Kawonne dereteththa qaaxon oothettishe diza gita dichcha oothota tamaare nayti yuuyi xeellana mala oothoy dic'c'iza gadaaddeti wodera dere dichcha ootho losetishe dic'c'ana mala ooththizaysi qonc'ettides.

Afrikka qeeri nayta boncho gallassa baala gaaso ooththidi Arba Minc'e yuusho woradan diza issi issi timirte keeththatappe shiiqida tamaareti Arba Minc'e salo sa'a deththa istaadoome oothoy diza deththa yuuyi xeellida.

Arba Minc'e: Hiisa 29, 2017(Gaammo Telebizhine):

Gaammo zoone mac'c'atanne qeeri nayta wuda kaaleththo kaappo M/ro Maammo Uruuta Afrikka qeeri nayta boncho gallassa baala gaaso ooththidi issi issi Arba Minc'e yuusho woradan diza timirte keeththatappe katamazan oothettishe diza gita istaadoome ootho xeelo qopobban shiiqida tamaareti dereteththa dichchateththa oge minthanaas wodera akeeka demmishe dic'c'ana mala mintheththiza lose dooridaysa qonc'issida.

Zoone gaaththan diza timirte keeththatan tamaariza tamaareti banta wolqa keena Arba Minc'e salo sa'a deththa naagida istaadoome ootho maaddishe dizaysa denthidi tamaareti oothoza banta ayfen xeellizaysi ooththiza maadozanne wodeppe dere dichcha minthos banta gisha minthidi kaaleththana mala dendoteththa medhdhees gida.

Ha gita pirojekitey kaalliza yeletas laatettiza pirojekite gidida gishshas qeera nayti attontan kumeththa dere kifileti maado minthidi kaaleththana mala xomosissida.

Afrikka qeeri nayta boncho gallassay Hiisa 25-ppe biidi Hiisa 29 gatho zoonezan diza enc'eretan qeera nayta maata bonchiso qopobban wuda woththida dumma dumma giigisotan bonchettishe gam'idaysa qonc'issida.

Yuuyi xeelo bessan Gaammo zoone mac'c'atanne qeeri nayta wuda kaaleththo kaappo M/ro Maammo Uruuta, Arba Minc'e yuusho worada mac'c'atanne qeeri nayta wuda xaafo keeththa kaapponne woradazan dumma dumma timirte keeththatappe shiiqida astamaaretinne tamaareti yametida.

የህፃናት ፓርላማ አባላት የአርባ ምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየም እያደረጉ ያሉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለፁየአፍሪካ የህፃናት ቀንን ምክንያት በማድረግ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የህፃ...
06/06/2025

የህፃናት ፓርላማ አባላት የአርባ ምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየም እያደረጉ ያሉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለፁ

የአፍሪካ የህፃናት ቀንን ምክንያት በማድረግ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ የህፃናት ፓርላማ አባላት የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ ሂደትን ጎብኝተዋል

የአርባ ምንጭ ዙርያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዝዋይ ደለለኝ የአፍሪካን የህፃናት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከ ጋሞ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ፣ አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት እና ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ጋር በጋራ የተዘጋጀ የጉብኝት መርሃ - ግብር መሆኑን አሳውቀዋል።

የአርባምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየም ሙሉ በሙሉ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚገነባ ህዝባዊ ፕሮጀክት መሆኑን የገለፁት ኃላፊዋ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚተላለፈውን ግዙፍ ግንባታ ለማጠናቀቅ ህፃናቱም እያደረጉ የሚገኙትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

የአፍሪካን የህፃናት ቀን ለሚቀጥሉት 5 ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ኩነቶች በሁሉም መዋቅር በድምቀት እንደሚከበር ጠቅሰዋል።

ዛሬ እየተከበረ የሚገኘውን የህጻናት የጉብኝት ቀንን ጨምሮ በአሉ በሚቀጥሉት አምስት ቀናት እንደሚከበር አብራርተዋል።

የአርባ ምንጭ አለም አቀፍ ስታዲየምን ሲጎበኙ ያገኘነው የቆላ ሸሌ 1ኛ ደረጃ ተማሪ የሆነው ጃፈር መሀመድ በጉብኝቱ ባየው ነገር መደሰቱን ጠቅሶ ሲያድግ በዚህ ስታዲየም የመጫወት ፍላጎት እንዳደረበት ሃሳቡን ሰጥቷል።

በተመሳሳይ መልኩ ሃሳቧን ያጋራችን የሸሌ ማዞሪያ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ተማሪ እታገኝ ግዛው እያደረጉ ያሉትን የገንዘብ ድጋፍ ግንባታው እስኪጠናቀቅ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግራለች።

በጉብኝቱ ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ የህፃናት ፓርላማ አባላት ተሳትፈዋል።

በህጻናት ላይ ለሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃትና በ...
24/05/2025

በህጻናት ላይ ለሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት በህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃትና በጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ ከወረዳው ቀበሌያት ለተወጣጡ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
ህፃናት የነገ ተስፋዎች ሀገር ተረካቢ እንደመሆናቸው ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ለህፃናት እድገት ተስፋቸውን ማለምለም እንዳለባቸውና እንዲሁም በባህል ተፅዕኖ ለሚደርስባቸውና ከሚደርስባቸው ማንኛውም ጥቃቶች መታደግ እንደምገባ አቶ ማቲዮስ መለሰ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አሰተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ተናግረዋል።
በዚህም ሂደት የሀይማኖት፣የሀገር ሽማግሌዎች ሚና የላቀ መሆኑን አቶ ማቲዮስ ጠቁመዋል።
በህፃናት ላይ የሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን መከላከል የአንድ ተቋም ስራ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገ ወ/ሮ ዝዋይ ደለልከኝ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ለሰልጣኞች ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል።
ወ/ሮ ዝዋይ አክለው በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ የተለያዩ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሁሉም ማህበረሰብ በመረባረብ ጥቃቱን ማስቆም አለበት ብለዋል።
በስልጠናው በወረዳው ከሚገኙ የቀበሌ መዋቅር የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት አባቶች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

አፋልጉንከዚህ በታች በፎቶዉ ላይ የምትመለከቱት ልጅ  ስሙ ኤፍሬም ካሳሁን ሹጋሮ፡ የእናቱ ስም ወ/ሮ መሰለች ማኬ የአባቱ ስም አቶ ካሳሁን ሹጋሮ ሲሆን የካቲት 20/6/2017 ዓ/ም ከአ/ምን...
02/05/2025

አፋልጉን
ከዚህ በታች በፎቶዉ ላይ የምትመለከቱት ልጅ ስሙ ኤፍሬም ካሳሁን ሹጋሮ፡ የእናቱ ስም ወ/ሮ መሰለች ማኬ የአባቱ ስም አቶ ካሳሁን ሹጋሮ ሲሆን የካቲት 20/6/2017 ዓ/ም ከአ/ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሼሌ ሜላ ቀበሌ ኤልጎ ንዑስ ከቤት እንደወጣ አልተመለሰም፡፡ ከዚህም የተነሳ እናቱ ተጨንቃ እያለቀሰች ስለምትገኝ እባካችሁ ልጁ ያለበት ቦታ የምታዉቁ ከዚህ በታች ባለዉ ስልክ ደዉላችሁ እንዲታሳዉቁን በእግዚአብሐሔር ስም እንለምናለን፡፡ 0916598485/0975709025/
0905451657/0942392850/0910932518

18/02/2025

የሴት ልጅ ጠለፋ የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት

መግቢያ
በሀገራችንም ሆነ በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የተለያዩ ወንጀሎች አሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ የጠለፋ ወንጀል ተጠቃሽ ነው፡፡ ይህ ወንጀል በ1996 ዓ.ም በወጣው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ በአምስተኛው መጽሀፍ በምዕራፍ 4 ርዕስ 2 ስር በሰው ነፃነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው ከተደነገጉት ውስጥ የሚመደብ የወንጀል ዓይነት ነው፡፡ ጠለፋ በሁለቱም ፆታዎች ላይ ሊፈፀም የሚችል ሲሆን በዋነኛነት በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚፈጸም ነው፡፡ በ1996 ዓ.ም የወጣው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ የጥቃትን መጠን እና አላማ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለጠለፋ ጥብቅ ተጠያቂነት ያስቀምጣል። የጠለፋ ድርጊቶችን ለመቀነስ ብሎም ለማስቀረት የተለያዩ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ለድርጊቶች ተጎጂዎች ጥበቃን የሚሰጡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ማፅደቅ፣ አገራዊ ህጎችን ማውጣት እንዲሁም ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች መስጠት ይገኙበታል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ ስለ ጠለፋ ምንነት፣ ጠለፋ ድርጊትን ሽፋን የሰጡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን፣ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት እና በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ ክልከላ የተደረገባቸውና የወንጀል ቅጣትን የሚያስከትሉ ድርጊቶችን እንመለከታለን፡፡

የጠለፋ ምንነት
ታዋቂው የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎው በ8ኛ እትሙ ጠለፋን ሲተረጉመው “The act of leading someone away by force or fraudulent persuasion” በሚል ሲሆን አንድን ሰው በማስገደድ ወይም በማጭበርበር ያለ ፈቃድ በማሳመን፣ በማጭበርበር ወይም በኃይል መውሰድ እንደሆነ አስቀምጦታል፡፡ ጠለፋ በወንጀል ህጋችን በግልጽ ትርጉም ባይሰጠውም በአውደ ጥበባዊ የህግ መዝገበ ቃላት ጠለፋ ማለት አንድን ሰው በጉልበት አፍኖ በመውሰድ እና በመደበቅ ገንዘብ ለማግኘት የሚደረግ ጥረት ነው። ሰውን የመጥለፍ ወንጀል ጽንሰ ሀሳብ ሰውን በጉልበት መውሰድ እና መደበቅ ነው፡፡ ጠለፋ በሀይል በተንኮል፣ በማታለል፣ በመጥለፍ የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ሲባል ሰውን/ሴትን መውሰድ ነው በሚል ተርጉሞታል፡፡

እንዴት ይፈጸማል
ጠለፋ አንዲትን ሴት በግዳጅ ጋብቻ ለማስፈጸም በማሰብ የሚደረግ ያለፈቃዷ ወደ ሌላ ቦታ የመውሰድና አስገድዶ የማቆየት ድርጊት ነው፡፡ይህ ድርጊት ከሴቷ እና ከቤተሰብ ፈቃድ ውጭ በማስገደድ የሚፈፀም ጋብቻ ነው፡፡ እንደሌሎች ጥቃት ሁሉ ድርጊቱ በሀገራችን በተለይም በገጠር አካባቢ ተስፋፍቶ የሚታይ ነው፡፡ የምትጠለፈው ሴት ድብደባ እና እንግልት ስለሚደርስባት ለአካል ጉዳት ወይም ሞት፣ ደስተኛ ያልሆነና ያልተረጋጋ ሕይወት (ጋብቻ) መኖር፣ ጭንቀት፣ ትምህርት (ሥራ ማቋረጥ) ወዘተ… የመሳሰሉትን ጉዳቶች ሊያስከትል ይችላል ፡፡ የጠለፋ ወንጀል በኢ.ፌዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ ከ587-588 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ወንጀሉ የሚከብደው ደግሞ በአንቀጽ 590 መሠረት ነው፡፡

ጠለፋ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች /ህግ እንዴት ይታያል
በተለያዩ የዓለም አቀፉ ስምምነቶች በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ጠለፋ አጥብቆ ያወግዛል። በነዚህ ዓለማቀፍ ስምምነቶች መሰረት ሀገራት በግዳጅ ጋብቻ፣ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች እና ሴቶችን ለወሲብ ንግድ በማሰማራት ምክንያት ጠለፋ ወንጀልን የመከላከል እና በህግ የመጠየቅ ግዴታ አለባቸው። ከስምምነቶቹም መካከል፡-
1. ሁሉን አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች መግለጫ (UDHR) አንቀጽ 3 እያንዳንዱ ሰው የሕይወት፣ የነፃነትና የደህንነት መብት አለው፡፡ እንዲሁም በአንቀጽ 2 ላይ "ማንኛውም ሰው በዘር፣ ቀለም፣ ጾታ፣ እና ሌሎች

28/12/2024

Address

Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbaminch Zuria Woreda Women & Children Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Arbaminch Zuria Woreda Women & Children Affairs Office:

Share