Bonke Woreda Government Communication Affairs Office

Bonke Woreda Government Communication Affairs Office B.W.C

ዮዮዮዮዮዮዮዮ.... ጋሞ ማስቃላ!......... ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣የ2015 ዓ.ም ዮዮዮዮዮዮ የጋሞ ማስቃላ ዘመን መለ...
25/09/2022

ዮዮዮዮዮዮዮዮ.... ጋሞ ማስቃላ!.........

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

የ2015 ዓ.ም ዮዮዮዮዮዮ የጋሞ ማስቃላ ዘመን መለወጫ የጋሞ መዲና በሆነችው በውበቷ አርባምንጭ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።

ጋዜሶ ፦መስከረም 15/2015 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

( #ዮዮዮዮዮዮ ማስቃላ!) የጋሞ ህዝቦች የዘመን መለወጫ በዓል ሲሆን በበዓሉ ላይ የኢፌዴሪ ፈዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ ክብር አቶ አገኘሁ ተሻግረን ጨምሮ ከተለያዩ ከኢትዮጵያ ክልሎች የተገኙ ተጋባዥ እንግዶች ፣የጋሞ ሀገር ሸማግሌዎች ፣በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የወረዳ መካከለኛ ባለሥልጣናት እና የአከባቢው ነዋሪዎች በፍቅር ፣በአንድነት እና ይበል በሚያሰኝ ሁኔታ በልዩ ድምቀት በዛሬው እለት አከብረዋል።

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ዮዮዮዮዮዮ..... ጋሞ ማስቃላ!፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ የዓርብ "ሶፌ " ገበያ በጋሞ ቦንኬ በከፍል ይንን ይመስላል። ጋዜሶ ፦መስከረም ...
23/09/2022

ዮዮዮዮዮዮ..... ጋሞ ማስቃላ!

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

የዓርብ "ሶፌ " ገበያ በጋሞ ቦንኬ በከፍል ይንን ይመስላል።

ጋዜሶ ፦መስከረም 13/2015 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በጋሞ ቦንኬ ከአመት አንዴ ብቻ የሚቆመው የዓርብ ገበያ ይህንን ይመስላል።

በዛሬው ዕለት ወደ አመሻሹ አከባቢ የ"ሶፌ " ሥነሥርዓት የሚከናወን ሲሆን ገበያተኞች ከቀኑ 10:00 ሰዓት አከባቢ የሚሸምቱትንም ሆነ የሚሸጡትን በማጠናቀቅ ለ"ሶፌ " መስቀል በዓል ቦታውን ይለቃሉ።

ወደ ገበያ መምጣት የጀመሩትም ከጧቱ 2:00 ጀምሮ ነበር።

ሰዎች( ለማስቃላ) በዓል ሲባል በዛሬው ገበያ የተለያዩ የአመት በዓል ዕቃዎችን ይሸምታሉ።

ዮዮዮዮዮዮ ጋሞ ማስቃላ!

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ዮዮዮዮዮዮ... ጋሞ... ማስቃላ!!፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣የጋሞ መስቀል በዓል እነሆ በ "ድቾ " ሥርዓት በ"ካሎ "ተጀምሯል።  ...
22/09/2022

ዮዮዮዮዮዮ... ጋሞ... ማስቃላ!!

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

የጋሞ መስቀል በዓል እነሆ በ "ድቾ " ሥርዓት በ"ካሎ "ተጀምሯል።

ጋዜሶ ፦መስከረም 12/2015 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

> > በማለት በጋሞ ቦንኬ የማስቃላ በዓል በ ከብቶች "ድቼ " ሥነሥርዓት ተጀምሯል።

በጋሞ ቦንኬ (ዮዮዮዮዮዮ ማስቃላ) የሚጀምረው በ"ድቼ " መሰቀል ሥርዓት ሲሆን ይህም በዕለተ ሐሙስ በዛሬው ቀን ልጆች ከብቶቻቸውን ወደ "ካሎ " በመውሰድ በይፋ በዓሉን አብስረዋል።

"ካሎ " ማለት መስቀል ሲደርስ ከብቶች የሚሰማሩበት ግጦሽ ማሳ ማለት ሲሆን የግጦሽ ማሳው ለአራት ወራት በአከባቢው ባህል መሰረት ምንም ከብት በግጦሹ እንዳይታገድ ተደርጎ በማቆየት በዛሬው ዕለት በከብቶች "ድቼ" ሀ ብለው መስቀል መጀመሩን ልጆች ያበስራሉ በማለት የቦንኬ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት አሳውቀዋል።

"ድቼ " በዕለተ ሐሙስ የሚከናወን ሆኖ የ(ጋሞ መስቃላ) በዓል የመጀመሪያው ቀን እና በዚህ ዕለት "ደሙፃ" ወይም ቃልቻ ተብሎ በአከባቢው ባህል መሰረት በሚጠራው ግለሰብ መሪነት ሁሉም የአከባቢው ህብረተሰብ የየራሱን ከብት ወደ " ካሎ"ው በመውሰድ ዙሪያ ዙሪያውን ብቻ እንዲያግዱ ወይም "ድቼ " እንዲፈጸሙ ይደረጋል ሲሉ የቦንኬ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ ክብር አቶ በየነ በዛብህ ገልጸዋል።

እንደ ዋና ሀላፊው አገላለጽ የ"ድቼ "ሥርዓት ለሁለት ቀናት የሚፈጸም ሆኖ በመጀመሪያው በዕለተ ዕሮብ የሚደረግ ሥርዓት እና የ"ደሙፃ" ወይም የ ቃልቻው እንስሳት በ "ካሎ "ው ጥግ ላይ የ"ድቼ" ሥርዓቱን ይፈጸማል ፤ በሁለተኛው ቀን ማለትም በዕለተ ሐሙስ የህበረተሰቡ እንስሳት ሁሉ የመጨረሻውን "ድቼ" ያደርጋል ብለዋል።

የ"ሶፌ " ጋሞ መስቀል በዓል በሚከበርበት በዕለተ ዓርብ የድቼ ሥርዓት ይጠናቀቃል ፤"ላአ" ወይም ሙሉ በሙሉ እንስሳትን በ"ካሎ"ው ወይም በግጦሽ ማሳው ውስጥ ይለቀቃል ፤ በዚሁ ዕለት ለከብቶችም ሆነ በአመቱ ለተጋቡ ሙሹሮች የ"ካጫ " ዎጋ ወይም ሥርዓት ይከናወናል ነው ያሉት ክብር ሀላፊው አቶ በየነ።

ክብር ሀላፊው አክለውም ለሰውም ሆነ ለእንስሳትና ለአእዋፍ ሁሉ የ"ካጫ " ቀን በ(ጋሞ ማስቃላ) ባህል መሰረት ይኖራል ፤ የ"ካጫ " ዎጋ በ"ሶፌ" ዕለት ለሰዎች እንዳለው ሁሉ በ"ካሎ " ለእንስሳትም ይኖራል ሲሉ ገልጸዋል።

የ"ሻንካ " ዎጋ ወይም ሥርዓት በዚሁ ዕለትም ይከናወናል ፤ከአሞጭና ከገብስ ወይም ከቦቆሎ ወ.ዘ.ተ የተዘጋጀ ቂጣ በእርጎ ወተት ልጆች ከብቶቹን ይዘው ወደ አመሻሽ አከባቢ ቤት ሲመለሱ በዕራት ሰአት ይቀርባል ፤ቤተሰብ በፍቅር አንድ ላይ ቀርበው ( ዮዮዮዮ... ማስቃላ! ፣ሀሹ ጋጌዛስካ! ፣ ዳናው... ዳናው ፣) እያሉ ይመገባሉ።

ዮዮዮዮዮዮዮ... ጋሞ ማስቃላ!
ዳናው............ ዳናው!
ገላኦይ ገሊ ውራናው ዳናው !...... ኢሊል ዙማዳ ዳናው!
ሀሬይ ካጨ ከሳናው ዳናው!

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

 Dubusha ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣በጋሞ ቦንኬ የ"ጎጎጃ  ዱቡሻ " ዕድሳት እየተከናወነ ይገኛል። ጋዜሶ ፦መስከረም 6/2...
16/09/2022

Dubusha

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

በጋሞ ቦንኬ የ"ጎጎጃ ዱቡሻ " ዕድሳት እየተከናወነ ይገኛል።

ጋዜሶ ፦መስከረም 6/2015 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በጋሞ ቦንኬ የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሆነውን የ እሴትና ባህላዊ ትውፊትን ጠብቆ ለማቆየት ሲባል የዕድሳት ሥራው እየተከናወነ ይገኛል።

"ዱቡሻ " በጋሞ ብሄረሰብ ለስብሰባ የሚጠቀሙበት ቦታ ሲሆን ለብሄረሰቡ ሸማግሌዎች እንደ ባህላዊ ስብሰባ አዳራሽ ያገለግላል።

ኢትዮጵያ ስለዲሞክራሲ ፣ስለመልካም አስተዳደር ፣ስለእርቅና ሰላም ከየትኛውም አገር ሳትበደር ጥቅም ላይ ስታዋል ከነበረባቸው መልካም ከሆኑ ባህላዊ እሴቶች አንዱ የ"ዱቡሻ " ስርዓት ነው ሲሉ የቦንኬ ወረዳ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ ክብር አቶ በየነ በዛብህ ገልጸዋል።

በ"ዱቡሻ" በሚደረግ የእርቅ ስነስርዓት ቀድሞ ጉዳዩን በዝርዝር የማስረዳት ሀላፊነት በዕድሜ ታላቅ (ባይራ) ከሆነው ወገን ይጀመራል። ይህንን ተፈጥሯዊና ጠቃሚ ባህልን ጠብቆ ለማቆየት ሲባል ማደስና የመንከባከብ ግዴታ በእኛ ትከሻ ላይ ተጥሎብናል ብለዋል ክብር ሀላፊው።

(ባይራዎች) ወይም ታላቅ የሆኑት ሸማግሌዎች በ"ዱቡሻ " ጠብና አለመግባባትን ፣ቂምና ቁርሾን በማስወገድ እርቅና አንድነትን ፣ሰላምና ፍቅርን ፣ልማትና ዕድገትን ስሰብኩ እኛ ደግሞ ወጣቶች ይህንን መልካም የሆነውን ባህላችን ለመጠቀም ብቻ ሳይሆን ለመጠበቅም መዘጋጀት አለብን ብለዋል።

በጋሞ ምድር ማህበራዊ ግጭቶች በ"ዱቡሻ "እየታከሙ አፋጣኝ ፈውስ እንዲያገኙ ይደረጋል። ለፀብ የተመዘዘ ሰይፎች አፎታቸው ለመግባት አይዘገዩም ሲሉ የቦንኬ ጋሞ ሀገር ሸማሌ አባል ካዎ ማጋርሳ አይማ ተናግረዋል።

በጋሞ ባህል መሰረት በ"ዱቡሻ " የማይፈታ አለመግባባት የለም አይኖርምም ያሉት ካዎ ማጋርሳ ይህን ስርዓት የመጠበቅም ሆነ የመንከባከብ ሀላፊነት አለብን ብለዋል።

በጋሞ ባህል መሰረት የ"ዱቡሻ " ስርአት ዘርፈብዙ ጠቀሜታዎችን ለህዝባችን ይሰጣል ሲሉ ያብራሩት እኝ የጋሞ ሀገር ሸማግሌ ካዎ ማጋርሳ በተለይ ዮዮዮ ማስቃላ በዓላትን ስናከብር "ባይራ" ወይም በኩር የሆኑት ሸማግሌዎች በዚህ ስፍራ ተሰባስበው ህጻናትን ፣ወጣቶችን ፣እናቶችን ፣ከብቶቻቸውን እና የዘሩትንና የተከሉትን ዕጽዋት ሳይቀር መልካም ፍሬ እንደሰጥና እንዲለማ በማሰብ ሁሉ ይመርቃሉ ብለዋል።

ዮዮዮዮዮዮዮ ማስቃላ በማለት በሁሉም ወገን ቂምን ረስቶ በእርቅ፣በይቅርታ ፣በሠላምና በአብሮነት ከክፉ ተግባርና ሀሳብ ወጥቶ በአዲስ መንፈስ ወደ አዲሱ አመት ለመሻገር ይቅር የሚባባሉበትም ስፍራ ነው "ዱቡሻ " ያሉት።

🌿🌿🌿🌿 ዮዮዮዮዮዮዮ ጋሞ ማስቃላ 💝🌻💝🌻💝

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ /ቤት ነው።

15/09/2022

መስከረም 5/2015

በ2015 ዓ.ም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ይሆናል - ትምህርት ሚኒስቴር
************************

በ2015 ዓ.ም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል) አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በተመሳሳይ፣ የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል አዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች በተመረጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሙከራ ትግበራ ይጀመራል ሲሉ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል በተለይ ለኢቢሲ ሳይበር ሚዲያ ገልጸዋል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የሙከራ ትግበራ ከሚካሄድባቸው ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ መምህራን ስርዓተ ትምህርቱን የማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠቱን ስራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰኞ መስከረም 9 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚጀመረው ትምህርት የተለያዩ ዝግጅቶች ማድረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ሰኞ እለት በይፋ ለሚጀመረው ትምህርት በአብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች የመክፈቻ ስነስርዓት እንደሚያካሄዱ ወ/ሮ አመለወርቅ ገልጸዋል ።

ተማሪዎች ደስ ብሏቸው የትምህርት ቀኑን እንዲጀምሩ የተለያዩ ዝግጅቶች በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚካሄድ የገለጹት ኃላፊዋ፣ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ በክልል ያሉ ትምህርት ቢሮዎች፣ ትምህርት ቤቶች እና የተለያዩ ድርጅቶች በትምህርት ቤት ውስጥ መዝናኛ ዝግጅት አዘጋጅተው ተማሪዎችን የመቀበል ስነ ስርዓት ያካሄዳሉ ብለዋል።

የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ መምህራንን እና ማህበረሰቡ በትምህርቱ የጊዜ ሰሌዳ እና በስርአተ ትምህርቱ አፈጻጸም ላይ ውይይቶችን እንዳደረጉ ወ/ሮ አመለወርቅ ጠቁመዋል።

ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ስራ ከመጀመራቸው በፊት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን ያወሱት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊዋ፣ በዚህም የትምህርት ቤቶች እድሳት፣ የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የመጽሐፍት ማስተዋወቅ እና የትምህርት ጉባዔ የማካሄድ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የቦንኬ ወረዳ አስተዳደር በዓሉን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ 🌱🌼🌱🌼🌱🌼🌱🌼🌱🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿አዲስ የሚንይዘው አመት የሠላምና ፍቅር ...
10/09/2022

የቦንኬ ወረዳ አስተዳደር በዓሉን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ

🌱🌼🌱🌼🌱🌼🌱🌼🌱🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿

አዲስ የሚንይዘው አመት የሠላምና ፍቅር ፤የፊሽታና ደስታ ፤የልማትና ዕድገት ፤የለውጥና ብልጽግና አመት ይሆንላችሁ ብለዋል ክብር አስተዳደር ተስፋጽዮን ዛቶ።

ጋዜሶ፦ጳጉሜ 5/2014 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

እንኳን ከ2014 ወደ 2015 ዓ.ም በሰላም አሸጋገራችሁ ሲሉ የገለጹት ክብር አስተዳዳሪው የመጪው አመት የደስታ አመት እንዲሆን ተመኝተዋል።

ባሳለፍነው አመት ኢትዮጵያና ህዝቦቿ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የገጠማት ፈተና ይሄ ነው የማይባል ቢሆንም ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር ውድና ድንቅ ስጦታ ሀገር ስለሆነች በዘር ሀረግ የነበራትን የአሸናፊነት ታሪኳን ይዛው ቀጥላለች።

አሸናፊነት በዘር ነውና ለኢትዮጵያ ሀገራችን ይህንን ሃያልነት ለአለም አስረግጣ ስታሳይ ትኖራለች።

ጁንታው ወያኔና ግብረአበሮቹ ይህችን ድንቅና ውድ ሀገር ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ያሰሩት ሴራ መቸም እንደማይሳካቸው ጀግናውና ክንዴ ብርቱ ጠላት ከፍቱ እንደጉም የሚተነው የመከላከያ ሀይላችን በተደጋጋሚ አስመስክረዋል ብለዋል ክብር አስተዳዳሪው።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ታርካዊ ቅብብሎሽ ረዥም አመት ያስቆጠረች ታርካዊ ሀገር ብቻም ሳትሆን ከረዥም አመታት ጀምሮ የገጠማትን ጠላት ሁለም ስታረፈርፈውና ስታርበደብደው ኖራለች ፤ይህም ታሪክ መለያዋ ነውና አብረው የሚኖራት ገድል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የዚህ ትልቁ ምስጢር በአንድነት በኢትዮጵያ ላይ የሚነሳውን ጠላት ለመከላከል መተባበራችን ፤ጥንትና ድሮም የነበረ የኢትዮጵያ አሸናፊነት እና ጀግንነት ፤ከአባቶቻችን ሲወርድና ሲዋረድ የመጣው ጀብዱነትና ወኔ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ክብር አቶ ተስፋጽዮን ዛቶ፦

ይሁን እንጂ ህዝባችን ቅን ነው ፤ጀግናና የልማት አርበኛ ህዝብ ነው ያሉት ክብር አስተዳዳሪው ፤አንድነትን ያውቃል ፤መተባበርና መደጋገፍ ለህዝባችን መለያው ነው። በመሆኑም ይህንን በዓል ስናሳልፍ የታረዙትን በማልበስ ፤የተራቡትን በማብላት ፤የተቸገሩትን በመደገፍና የተከፋውን በማጽናናት በመቻቻል ባህላችን ልሆን ይገባል ብለዋል።

ጀግናዎችና አይበገረዎቹ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በዚህን ጊዜ ዝናቡ ሳይበግረው በዱር ገደሉ በመሆን የእናት ጡት ነካሾችን አየተፋለመና ኢትዮጵያን እየተከላከሉ መገኘታቸውን በማሰብ የሞራልም ሆነ የስንቅ ድጋፍ በማቀበል ማሳለፍ ይጠበቅብናል ብለዋል።

በወረዳችም ውስጥ ተጠናክሮ የቀጠለውን ልማት ከጀግናው ህዝባችን ጋር በመተባበር በተሻለ ሁነታ በማስቀጠል የተሻለ ልማት ለማከናወን የሚንሰራበት አመት ልሆን ይገባል ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው።

አዲሱ አመት የደስታና የሰላም እመት ይሆንልን ሲሉ በድጋሚ አሳስበዋል ክብር ዋና አስተዳደሩ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ትኑር!!

🌿🌼🌿🌼🌿🌼😳🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼🌿🌼

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የልማት አርበኛው ዳዳና አርሼ ቦንኬ ለሀገር መከላከያ የሠንጋ በሬና ምግብ ነክ ዕቃዎችን ሽኝት አደረገ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣በጋሞ...
08/09/2022

የልማት አርበኛው ዳዳና አርሼ ቦንኬ ለሀገር መከላከያ የሠንጋ በሬና ምግብ ነክ ዕቃዎችን ሽኝት አደረገ

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

በጋሞ ዞን በቦንኬ ወረዳ ለጀግናው ሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚደረገውን ድጋፍ ወደ ግንባር የመላክ ሽኝት ተደርገዋል።

ጀግናው ህዝባችን በኢትዮጵያዊነት የማይደራደረው 14= ሠንጋ በሬ ፣27= በግ ፣ስድስት ኩንታል ሰምባች ምግብ እና የተለያዩ ምግብ ነኮችን ነበር ድጋፍ ያደረገው።

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለጀግናው ሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ጋዜሶ ፦ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም (የቦን...
08/09/2022

ለጀግናው ሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

ጋዜሶ ፦ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በጋሞ ዞን በቦንኬ ወረዳ ለጀግናው ሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

የእናት አገር ኢትዮጵያን ሉአላዊነት እና ክብሯን ጠብቀው ፤ለህዝቦቿ ነፃነት እና እኩልነት ለሚታገሉት ለጀግናው መከላከያ የሚደረግ የትኛውም አይነት ድጋፍ የሚያንስ እንጂ የሚበዛ እንዳለሆነ አስተያየት ሰጪዎች እየገለፁ ይገኛሉ።

በወረዳው ውስጥ የሚገኙ አስራ አንድ ቀበሌያት በሙሉ በከፍተኛ ወኔ ተነሳስተው አንዳንድ የሠንጋ በሬ ፣በግ እና የተለያዩ ምግብ አይነቶችን በማቅረብ ደጀንነታቸውን እያሳዩ ይገኛሉ።

የወረዳው መንግስት ሰራተኞች በአይነትና በገንዘብ የሚያደርጉትን ትብብር አጠናክሮ ቀጥለውበታል።

ኢትዮጵያን ፦እናልማ ፣እንገንባ ፣እንዘጋጅ

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!



ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ /ቤት ነው።

07/09/2022
ዮዮ ጋሞ ማስቃላ ከ"ሶፌ" ሥርአት በጥቅቱ ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ጋዜሶ ፦ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚ...
07/09/2022

ዮዮ ጋሞ ማስቃላ ከ"ሶፌ" ሥርአት በጥቅቱ

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

ጋዜሶ ፦ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በጋሞ ቦንኬ መስቀል መሰረት በዓመቱ ውስጥ በትዳር ለተሳሰሩ ጥንዶች “የሶፌ” ሥርዓት የሚፈፀመው በአመት አንድ ጊዜ በሚቆመው በአርብ ጮሻ ገበያ ዕለት ይሆናል።

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ጳጉሜ 02 የ"አምራችነት" ቀን ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣የዘንድሮው ጳጉሜ 02/የ"አምራችነት "ቀን በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ ስ...
07/09/2022

ጳጉሜ 02 የ"አምራችነት" ቀን

፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣

የዘንድሮው ጳጉሜ 02/የ"አምራችነት "ቀን በሚል መሪ ቃል በሀገር ደረጃ ስዘከር ይውላል።

ጋዜሶ ፦ጳጉሜ 2/2014 ዓ.ም (የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የዘንድሮው ጳጉሜ 2 የሚታሰብበት ዋና ዐላማው የኢንዱስትሪ ፣የግብርና ፣የትራንስፖርት እና በሎጂስቲክ ዘርፉ የተመዘገቡ ድሎችን እና ተግዳሮቶችን በመለየት ለቀጣይ አመት በሀገር ደረጃ ዝግጅት የሚደረግበት ቀን በመሆኑ ይህ ቀን ይታሰባል።

ዘገባው የቦንኬ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

Address

Bonke Woreda
Arba Minch'

Telephone

+251939614596

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonke Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share