Ankober woreda Communication affairs office

Ankober woreda Communication affairs office A leading role in the Queen's Communication Information Sector: Integrating our vision for the succes

የዓለም የአካባቢ ቀን በሀገራችን ግንቦት 28/2018 በተለያዩ ኩነቶች ይከበራል።ግንቦት 27/2018አዲስ አበባ============የዓለም የአካባቢ ቀን በየዓመቱ ግንቦት 28 ይከበራል፡፡ የዘ...
03/06/2026

የዓለም የአካባቢ ቀን በሀገራችን ግንቦት 28/2018 በተለያዩ ኩነቶች ይከበራል።
ግንቦት 27/2018
አዲስ አበባ
============
የዓለም የአካባቢ ቀን በየዓመቱ ግንቦት 28 ይከበራል፡፡ የዘንድሮ የዓለም አካባቢ ቀን “Climate Action’’ በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ይከበራል።

የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ሁኔታ እና የበአሉ አስፈላጊነትን በተመለከተም ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት የምታበረክተው አስተዋጽኦ ከ 0.5% በታች ቢሆንም፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለሚከሰቱት ተደጋጋሚ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የመሬት መንሸራተት፣ የደን መመናመንና የመሬት መራቆት በእጅጉ ተጋላጭ ናት። እነዚህ ተግዳሮቶች በዝናብ ጥገኛ በሆነው ግብርና፣ በምግብ ዋስትና፣ በውሃ ሀብታችን እና በገጠሩ ማኅበረሰብ የኑሮ ሁኔታ ላይ ቀጥተኛ ስጋት ደቅነዋል። በመሆኑም “Climate Action’’የሚለው መሪ ቃል ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም ያለው። የአገራችን አየር ንብረት ለውጥ ምላሽ በሚከተሉት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትክረት በማድረግ እየተሰሩ ይገኛሉ፦
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር፦ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ኢትዮጵያ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኑን ወደ 23.6% አሳድጋለች።

የ2018 ዓ.ም ትኩረታችን የችግኞችን የመጽደቅ መጠን ማሻሻል፣ ዘላቂ የተፋሰስ ልማት እና የረጅም ጊዜ ሥነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን ማረጋገጥ ላይ ነው።
የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና እና የውሃ ልማት፦ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወደ አፈር ጥበቃ፣ መስኖ ማስፋፋት እና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም (climate-smart) አሠራሮች መሸጋገር።
ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ/የሐይል ምንጭ ሽግግር፦ ከ95% በላይ ታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ስኬታችንን መሰረት በማድረግ፣ ንጹህ ኃይልን ወደ ትራንስፖርት እና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ማስፋፋት።
የከተሞች ጽዳትና ውበት፦ የቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እና የከተማ አረንጓዴ መሠረተ-ልማትን ማጠናከር እና ከከተሞች የሚወጣውን የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት በመቀነስ።

ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋሚያ ፋይናንስ፣ ለቴክኖሎጂ ሽግግር እና ለእውቀት ማሳደግ አጋርነትን ማጠናከር።
የዘንድሮ የዓለም አካባቢ ቀን ሲከበርም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም መላው የህብረተሰብ ክፍል የሚከተሉትን ተግባራት ከግምት ውስጥ በማስገባት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ችግኞችን መትከል እና መንከባከብ።
ዘላቂ የቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ ሥርዓትን መከተል።
የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን ላይ በንቃት መሳተፍ።
ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ እና የሚበሰብሱ የእቃ መያዣዎችን በመጠቀም፡፡
ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋሚያ ፋይናንስ፣ ለቴክኖሎጂ ሽግግር እና ለእውቀት ማሳደግ አጋርነትን ማጠናከር።
የአካባቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ግንዛቤዎችን ማስፋፋት፡፡
በወንዝ ዳርቻ ልማት እና በኮሪዶር ማስፋፊያ ስራዎች የተገኙ ውጠየቶችን ለመጠበቅ እና ለማስፋት በሚደረግ ርብርብ ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግ፡፡
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
ጽዱ ኢትዮጵያ ባህል እናደርግ

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"         ክቡር አረጋ ከበደየአማራ ክልል ርእ...
03/06/2026

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"

ክቡር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር

03/06/2026

Check out ankober communication’s video.

03/06/2026
የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁየአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ምርጫውን አ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተሳትፎ እና በስኬት መጠናቀቁን የአንኮበር ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት  ገለጸ።  አንኮበር ፦ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም (አንኮበር ኮሙኒኬሽን) በሰሜን ሸዋ ዞን በ...
02/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተሳትፎ እና በስኬት መጠናቀቁን የአንኮበር ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለጸ።

አንኮበር ፦ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም (አንኮበር ኮሙኒኬሽን) በሰሜን ሸዋ ዞን በአንኮበር ምርጫ ክልል የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ሰላማዊ እና ፍትሐዊ በኾነ መንገድ መጠናቀቁን የአንኮበር ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለጸ።

የጽ/ቤቱ ፖሊስ አዛዥ ም/ል ኢንስፔክተር አብራራው ማስረሻ እንዳሉት በጎረቤላና አልዩ አምባ ከተማ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማስተጓጐል ጽንፈኛው ዙሪያውን ሲተኩስ ቢውልም ያሰበው ሳይሳካለት ምርጫውን ማኅበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ በመምረጥ ማኅበረሰቡ ከመንግሥት ጎን መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ሕዝቡ ለመምረጥ ያሳየው ትጋት እጅግ የሚበረታታ ነበር፤ መራጩ ሕዝብም ያለምንም ጫና ድምጽ መስጠቱን ተናግረዋል።

ኃላፊው ለምርጫው መሳካት ገለልተኛ በመኾን በብርታት ለሠሩ የጸጥታ መዋቅር፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ለአስፈጻሚዎች እና ለመላው ሕዝብ የላቀ ምሥጋና አቅርበዋል።

ከጽንፈኞች በተተኮሰ የዲሽቃ ጥይት የመንቶች እናትና ነፍሰ ጡሯ ወ/ሮ ፋጡማ አቦዬ ሕይወቷ አለፈ።   ነዋሪነቷ በአንኮበር ወረዳ አልዩ አምባ ከተማ የሆነችው ወ/ሮ ፋጡማ አቦዬ በሽር 7ኛውን ...
02/06/2026

ከጽንፈኞች በተተኮሰ የዲሽቃ ጥይት የመንቶች እናትና ነፍሰ ጡሯ ወ/ሮ ፋጡማ አቦዬ ሕይወቷ አለፈ።

ነዋሪነቷ በአንኮበር ወረዳ አልዩ አምባ ከተማ የሆነችው ወ/ሮ ፋጡማ አቦዬ በሽር 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለመሣተፍ እየሄደች ባለችበት ከጽንፈኞች በተተኮሰ የዲሽቃ ጥይት መተኪያ የሌለውን ውድ ሕይወቷን ማጣቷን ከስፍራው የደረሠን መረጃ ያመለክታል።

የጽንፈኛ ቡድኑ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማስተጓጐል ወደ ሕዝቡ እና ወደ መኖሪያ ቤታቸው ዲሽቃ በመተኮስ ሙሉ ቀን ሲደበድብ ውሏል። በዚህም የሕዝብ ጠላት መሆኑን በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት በአማራ ክልል አድማ መከላከል የ29ኛ ሻለቃ ም/ል አዛዥ ም/ል ኢንስፔክተር አማረ አሰፋ።

እንደ ኃላፊው ገለጻ ጽንፈኛው ለሕዝብ እሞታለሁና እታገላለሁ ቢልም፤ ነገር ግን በተግባር ሲታይ ከሕዝብ እየዘረፈ እና ንጹሐንን እየገደለ የሚኖር በአደባባይም አሸባሪ ሌባ መሆኑን ሕዝቡ ተረድቶታል ብለዋል።
ዛሬ በአልዩ አምባ ከተማ ልዩ ቦታው መደብር በተባለ ቦታ ነዋሪ የሆነችውን የመንቶች እናትና ነፍሰ ጡሯ ወ/ሮ ፋጡማ አቦዬ ጽንፈኛው በተኮሰው የዲሽቃ ጥይት ገድሏል። ሙሉ ቀንም ወደ ከተማ ዲሽቃ በመተኮስ የማኅበረሰቡን ቤት ሲደበድብ ውሏል ነው ያሉት ኃላፊው።

በተመሣሣይ በጎረቤላ ከተማ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማስተጓጐል ዙሪያውን ሲተኩስ ቢውልም ያሰበው ሳይሳካለት ምርጫውን ማኅበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ በመምረጥ ማኅበረሰቡ ከመንግሥት ጎን መሆኑን በተግባር አሳይቷል።

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው"‎‎በአንኮበር  ወረዳ አልዩ አምባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ ቀበሌዎች  የሚገኙ መራጮች በማለዳው ወጥተው ድምፃቸውን እየሰጡ ነው።‎
01/06/2026

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው"

‎በአንኮበር ወረዳ አልዩ አምባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ መራጮች በማለዳው ወጥተው ድምፃቸውን እየሰጡ ነው።

Address

Amhara Region North Shewa
Ankober
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ankober woreda Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ankober woreda Communication affairs office:

Share