የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ/Konta Zone Justice Department

  • Home
  • Ethiopia
  • Ameya
  • የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ/Konta Zone Justice Department

የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ/Konta Zone Justice Department We stand for truth and Justice⚖️

02/04/2026

ከ60 ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 ሆኖ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸደቀ!
**************************
የ1954 የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕጉ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየ በመሆኑ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግሥት፣ በ1997 ከወጣው የወንጀል ሕግ፣ ሀገራችን ከምትተገብረው የወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዘርፉ ካሉ አዳዲስ አሠራሮችና የቴክኖሎጂ እድገቶች አኳያ ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ መልኩ መከለሱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ባለፉት ዓመታት የአዲስ ሕግ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል። ዛሬ የጸደቀው የሕግ መድብል አዳዲስ አሠራሮችን ከማስተዋወቁ በተጨማሪ የማስረጃ ሕግ በማካተት በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የቆየውን አንድ ትልቅ ክፍተት ለመሙላት አስችሏል። ሕጉ የወንጀል ምርመራ፣ ክስና ማስረጃ ሥርዓቱን ወደአዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው።

የወንጀል ሥነ ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በማርቀቅ ሂደት ከ15 ዓመታት በላይ የወሰደ ሲሆን ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተለዩ ቁልፍ የሕግ ሪፎርሞች አንዱ ሆኖ፣ ብዙ ምክክር ተደርጎበት ሊጸድቅ ችሏል። ሕጉ ሀገር አቀፍ ተፈጻሚነት ያለው ሲሆን ከዚህ ሪፎርም የሚጠበቀውን ውጤት እውን ለማድረግ የፍትሕ ሚኒስቴር በሁሉም ደረጃ ከሚገኙ የፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት ይሠራል።

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701...
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_external

በኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ የኤች አይቪ/ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ተካሄደ።   መጋቢት 23/2018 ዓ.ም ኮንታ_አመያየግንዛቤ ማስጨበጫው የተሰጠው ለአጠቃላይ የመምሪያው ሠራተኞች ሲሆ...
01/04/2026

በኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ የኤች አይቪ/ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ተካሄደ።
መጋቢት 23/2018 ዓ.ም ኮንታ_አመያ
የግንዛቤ ማስጨበጫው የተሰጠው ለአጠቃላይ የመምሪያው ሠራተኞች ሲሆን በአቅራቢያ የሚገኙ የሌላ መ/ቤት ሠራተኞችም እንዲሳተፉ መደረጉም ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ የፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ተፈራ የተገኙ ሲሆን የመምሪያው ኃላፊ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሰለ ኤች አይ ቪ አስከፊነት፣ መከላከልና ተጎጂዎችን መርዳት በተመለከተ የሚሰጠው ትኩረት ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መምጣቱን ገልፀው በዚህም ምክንያት የቫይረሱ ስርጭት እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ሁሉም ሰው ቫይረሱን ከመከላከልና ተጎጂ ዜጎችን ከመደገፍ አንፃር የድርሻውን መወጣት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።
ስልጠናውን የሰጡት የጤና ባለሙያ የሆኑት አቶ ዘሪሁን ብርሃኑ ስለ ቫይረሱ ምንነት፣ስለመተላለፊያ መንገዶችና ስለመከላከያ መንገዶች እንዲሁም ስለአጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታዎች በዝርዝር አቅርበው ግንዛቤ አስጨብጠዋል። በውይይቱም የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበው መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ተደራሽና ተዓማኒነት ያለው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጥ አገልግሎት በወረዳና ከተማ ...
27/03/2026

የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ፣ ተደራሽና ተዓማኒነት ያለው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጥ አገልግሎት በወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ላይ ለማስጀመር የሚያስችል ስልጠና ሰጥቷል።

የስልጠና መድረኩን የመሩት የዞኑ ም/አስተዳዳሪና ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ወጁ እንደገለፁት የሰነዶችን ምዝገባና ማረጋገጥ አገልግሎት አሰጣጥ በቅንጅትና በባለቤትነት ስሜት መምራት ያስፈልጋል ብለዋል።

ተግባሩ እጅግ ወሳኝ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ያሉት አቶ ወንድማገኝ ተቋማት ተናበው በመሥራት የህብረተሰቡን መብትና ጥቅም ማረጋገጥ ላይ አጽንኦት መስጠት ይጠበቅባቸዋል ሲሉ ገልፀዋል።

የስልጠናውን ሰነድ ያቀረቡት የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ተፈራ በበኩላቸው በፍትህ ተቋም ከሚሰጡ መጠነ ሰፊ አገ/ቶች ውስጥ አንዱ የሰነድ ምዝገባና ማረጋገጥ መሆኑን ገልፀዋል።

ኃላፊው አያይዘውም አገልግሎቱ ከዚህ ቀደም በዞን ደረጃ ብቻ የተወሰነ በመሆኑ ሩቅ አካባቢ ያሉ የተለያዩ የህ/ሰብ ክፍሎች ሲቸገሩ መቆየታቸውን አውስተው አሁን ላይ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ የሰነድ ምዝገባና ማረጋገጥ አገልግሎት መመሪያ ቁጥር 33/2018 እንዲወጣ ማድረጉን ተከትሎ ህ/ሰቡ በያለበት መዋቅር አገልግሎቱን በቅርበት እንዲያገኝ የሚያስችል ዕድል መፈጠሩን ገልፀዋል።

አያይዘውም የሰነድ ምዝገባና ማረጋገጥ ሥራ በዋናነት በዜጎች ሀብትና ንብረት ባለቤትነት ላይ ዋስትና የሚሰጥ ጉዳይ በመሆኑ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።

መመሪያው ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ተዓማኒነት ያለው አገ/ት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ ግልጽ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረው በትግበራ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ባለድርሻ አካላት ተናበው መስራት አለባቸው ብለዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ለወደፊት ስራቸው አቅም የሚፈጥር ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀው ተግባሩን ውጤታማ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር፣ የግብዓትና የሰው ኃይል እጥረት ችግሮችን መቅረፍ እና ችግር ፈቺ የሆነ ድጋፍና ክትትል ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በስልጠናው መድረክ ላይ የዞኑ ም/ል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ወጁ፣ የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ተፈራን ጨምሮ የ5ቱም መዋቅሮች የፍትህ እና የገቢ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የዞንና የወረዳ አቃቤያን ህጎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው!

ማስታወቂያ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ለህግ ባለሙያዎች👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
30/01/2026

ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ለህግ ባለሙያዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

በኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ ድጋፋዊ ክትትል ተደረገ።  22/5/2018 ዓ.ም ኮንታ-አመያ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የ2018ዓ/ም ግማሽ አመት አፈጻጸም በተመለከተ የተ...
30/01/2026

በኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ ድጋፋዊ ክትትል ተደረገ።
22/5/2018 ዓ.ም ኮንታ-አመያ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የ2018ዓ/ም ግማሽ አመት አፈጻጸም በተመለከተ የተከናወኑ ተግባራት ላይ ያተኮረ ድጋፋዊ ክትትል በኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ ተደርጓል።
የድጋፍ ክትትል ያደረጉት የኮንታ ዞን ፐ/ሰ/ሰ/ሀ/ል/መምሪያ የመ/አስ/ር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ታገል እሸቱ እና የሪፎርም ጉዳዮች ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ በተዘጋጀው ቼክ-ሊስት መሰረት የተቋሙን አፈፃፀም የገመገሙ ሲሆን ከተነሱት አንኳር ነጥቦች መካከልም ተቋማዊ ዕቅድና አፈጻጸም፣ የመልካም አስ/ር ዕቅድ አፈፃፀም፣ የቲም ውይይት፣ የዜጎች ቻርተር፣ ፈጣን ለውጥ ማምጫ መሳሪያዎች፣ ቅሬታ አፈታት፣ ፀረ ኪራይ ሰብሳቢነት፣ ቅንጅታዊ አሰራር፣ የሰራተኛ ጥቅም፣ የጡረታ መረጃ ጉዳዮች ተነስተው በሰፊው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ተፈራ ተቋሙ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ መሆኑን ገልፀው የተለያዩ መረጃዎችንና ሰነዶችን በማቅረብ አፈፃፀሙን አብራርተዋል።
የማኔጅመንት አካላትም በየሥራ ሂደታቸው የተሰሩትን ሥራዎች በሚገባ ገለፃ አድርገዋል።
የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ ታገል እሸቱ እንደገለፁት ተቋሙ ከላይ ከተነሱት ነጥቦች አንፃር በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ ያለ መሆኑን ገልፀው እነዚህን መልካም ነገሮችን አጠናክሮ እንዲቀጥል እና በጉድለት የተነሱ ጉዳዮችን የዕቅድ አካል በማድረግ መሥራት እንደሚገባ በማሳሰብ ውይይቱ ተጠናቋል።

ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዓል በኮንታ ዞን ፍትሕ መምሪያ ተከበረ።17/03/2018 ዓ.ም ኮንታ አመያ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስ...
27/11/2025

ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዓል በኮንታ ዞን ፍትሕ መምሪያ ተከበረ።
17/03/2018 ዓ.ም ኮንታ አመያ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዓል "ትውልድን በስነ-ምግባር፣ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በኮንታ ዞን ፍትሕ መምሪያ ተከብሯል።
በዓሉን የ3(ሦስት) ተቋማት ሠራተኞች በጋራ በመሆን ያከበሩ ሲሆን እነዚህም የዞኑ ፍትሕ መምሪያ፣ የዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት እና የዞን ሠላም፣ፀጥታና ሚሊሻ መምሪያ መሆናቸው ታውቋል።
በዕለቱ በዓሉን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞን ሠላም፣ፀጥታና ሚሊሻ መምሪያ ተወካይ የሆኑት አቶ አያሌው ከበደ በንግግራቸው ሙስና የአንድን ሀገር ኢኮኖሚ በእጅጉ የሚጎዳ እና የትውልድ ገዳይ በመሆኑ ሁሉም ሠራተኛ አምርሮ ሊታገለው ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዕለቱ በዓሉን በማስመልከት የመወያያ ሰነድ የዞን ፍትህ መምሪያ ተወካይ በሆኑት አቶ ሀብታሙ ሀደሮ የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ላይ ሰፊ ውይይትም ተደርጓል።
በዕለቱም በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀ ግጥም እና አስተማሪ ታሪኮችም ለተሳታፊዎች ቀርበዋል።
ውይይቱንም የዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዘላለም ግዛው ከሌሎች የመምሪያዎች ተወካዮች ጋር በጋራ የመሩ ሲሆን ከሠራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል።
ዘገባው የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ ነው።

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች          ክፍል 4 (የመጨረሻ ክፍል) ========================የቀጠለ........ስለዚህም ክስ ወይም ቅጣት የታገደበት ወይም የተቋረጠበት ምክንያት ...
21/08/2025

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች
ክፍል 4 (የመጨረሻ ክፍል)
========================
የቀጠለ........
ስለዚህም ክስ ወይም ቅጣት የታገደበት ወይም የተቋረጠበት ምክንያት ምንም ይሁን ምን: ፍፁም የሆነው የይርጋ ዘመን ከተጠናቀቀበት ቀን ጀምሮ ወንጀል በፈፀመ ሰው ላይ ክስ መመስረት ወይንም ቅጣት በተወሰነበት ሰው ላይ ቅጣት እንዲፈፀም ማድረግ አይቻልም።
የክስ ማቅረቢያ ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የመደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን አጠፌታ፣ ወይም በግል አቤቱታ የሚቀርብ የወንጀል ጉዳይ ዓይነት ሲሆን የግል አቤቱታ ልዩ የይርጋ ዘመን ከአጋማሽ የሚበልጥ ጊዜ ሲያልፍ ነው። ከዚህ አንፃር ለምሳሌ፦ ከአንድ ዓመት በላይ ቀላል እሥራት የማያስቀጣ ወንጀል መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን 5 ዓመት ነው። ፍፁም የሆነ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመኑ ግን የመደበኛው አጠፌታ ማለትም የአምስት ዓመት አጠፌታ ስለሚሆን 10 ዓመት ነው ማለት ነው። እንዲሁም ልዩ የግል አቤቱታ ማቅረቢያ መደበኛ የይርጋ ዘመኑ 2 ዓመት ነው። ነገር ግን ልዩ የግል አቤቱታ ማቅረቢያ ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን ግን የመደበኛ የይርጋ ዘመን ከአጋማሽ የሚበልጥ ጊዜ ሲያልፍ፡ ማለትም የ2 ዓመት አጋማሽ ሲያልፍ ስለሚሆን 3 ዓመት ነው ማለት ነው። የቅጣት እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን አለፈ የሚባለው ከመደበኛው የቅጣት የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ ነው። በዚህም መሠረት ለምሳሌ ከአንድ ዓመት በላይ ከአስር ዓመት በታች ለሆነ ነፃነት የሚያሳጣ ቅጣት የተደነገገው መደበኛ የቅጣት ይርጋ ዘመን 10 ዓመት ነው። በመሆኑም ለእንደዚህ ዓይነት ቅጣቶች የሚኖረው ፍፁም የሆነ የቅጣት የይርጋ ዘመን ከመደበኛው በግማሽ የሚበልጥ በመሆኑ ከአስር ዓመት በግማሽ የሚበልጥ ማለትም 15 ዓመት ይሆናል ማለት ነው።
ስለተከታተላችሁን እናመሰግናለን!

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች          ክፍል 3 ========================የቀጠለ.......የቅጣት ይርጋ ዘመን መቆጠር የሚጀምረው መቆጠር ከጀመረ በኋላም እንዲሁ በተለያዩ ምክንያ...
18/08/2025

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች
ክፍል 3
========================
የቀጠለ.......
የቅጣት ይርጋ ዘመን መቆጠር የሚጀምረው መቆጠር ከጀመረ በኋላም እንዲሁ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ሊታገድ ወይም ሊቋረጥ ይችላል።በወንጀል ህጉ አንቀጽ 227 ላይ እንደተመለከተው በወንጀለኛው ላይ የተጣለውን ቅጣት የማስፈፀም ኃላፊነት ባለው አካል ቅጣቱን ለማስፈፀም የሚደረግ ማናቸውም ተግባር የቅጣት ይርጋ ዘመን መቆጠር እንዲቋረጥ የማድረግ ውጤት አለው። በሌላ በኩል የቅጣት ይርጋ ዘመን መቆጠር ታግዶ የሚቆይባቸው ሁኔታዎች በወንጀል ህጉ አንቀጽ 226 ላይ ተመላክተዋል። እነርሱም በወንጀለኛው ላይ የተጣለውቅጣት እንዳይፈፀም ወይም አፈፃፀሙ ተጀምሮ ከሆነ እንዳይቀጥል የሚያደርግ ምክንያት ተከስቶ ከሆነ ይህ መሰናክል እስኪወገድ ድረስ በተቀጪው ላይ የተጣለው ቅጣት ታግዶ በአመክሮ ተፈትቶ፣ የዕዳ መክፈያ ጊዜ ተሰጥቶት ከሆነ ይህ የተሰጠው ጊዜ እስኪያልቅ፣ ተቀጪው ታስሮ ከሆነ እስሩ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ የቅጣት ይርጋ ዘመን መቆጠሩ ታግዶ ይቆያል። የጥንቃቄ እርምጃዎች ያለ ዋነኛ ቅጣት በሚወሰኑበት ጊዜ በይርጋ ቀሪ ሊሆኑ የሚችሉበት ዘመን በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ላይ አልተመለከተም። አሁን ግን በአዲሱ የወንጀል ህግ አንቀጽ 224(1) ስር እንዲገባ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የጥንቃቄ እርምጃዎች መደበኛ የቅጣት ይርጋ ዘመን አምስት አመት ሆኗል።
3. የመደበኛ እና ፍፁም የይርጋ ጊዜ ልዩነት
ለወንጀል ጉዳዮች የሚውል የይርጋ ጊዜ ሁለት ዓይነት ነው። አንደኛው መደበኛ የይርጋ ጊዜ የሚባለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ፍፁም የይርጋ ጊዜ የሚባለው ነው። ከዚህ በላይ በቀረበው ጽሑፍ ላይ የይርጋ መቆጠርን የሚያግዱ ወይም የሚያቋርጡ ሁኔታዎች ስለመኖራቸው ተመልክተናል። እነዚህ ምክንያቶች በሚኖሩበት ጊዜ የይርጋ መቆጠር ታግዶ ወይም ተቋርጦ የሚቆይ ሲሆን ሁኔታዎቹ ሲወገዱ ወይም ሳይኖሩ ሲቀር ደግሞ የይርጋ ዘመን እደገና መቆጠር ይጀምራል። ነገር ግን እነዚህ ሁኔታዎች እንዲህ ዓይነት የማገድ ወይም የማቋረጥ ውጤት(Effect) የሚኖራቸው በመደበኛው የይርጋ ጊዜ ላይ ነው። ፍፁም የሆነ የይርጋ ጊዜ መቆጠር ከጀመረ በኋላ በምንም ዓይነት ምክንያት ሊታገድ ወይም ሊቋረጥ አይችልም። በዚህም መሰረት ፍፁም የሆነ የይርጋ ጊዜ በሚቆጠርበት ጊዜ የይርጋ ዘመን መቆጠርን የሚያግዱ ወይም የሚያቋርጡ ሁኔታዎች በፍፁም ግምት ውስጥ አይገቡም። ..........ይቀጥላል

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች          ክፍል 2 ========================የቀጠለ.......ለምሳሌ ተከሳሹ ያለመከሰሰ መብት ያለው ቢሆን (ህጋዊ መሰናክል ) ወይም ደግሞ ተከሳሹ ...
14/08/2025

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች
ክፍል 2
========================
የቀጠለ.......
ለምሳሌ ተከሳሹ ያለመከሰሰ መብት ያለው ቢሆን (ህጋዊ መሰናክል ) ወይም ደግሞ ተከሳሹ በፅኑ ቢታመም (የፍሬ ነገር መሰናክል ) ይህ መሰናክል እስኪወገድ ድረስ የይርጋ ዘመን መቆጠሩ ታግዶ የሚቆይ ሲሆን መሰናክሉ እንደተወገደ መቆጠር ይጀምራል። ይህም በሚሆንበት ጊዜ መሰናክሉ ከመከሰቱ በፊት የተቆጠረው ጊዜ ከቀሪው ዘመን ጋር እንዲታሰብ ይደረጋል። በሌላ በኩል ወንጀለኛውን ለመያዝ ለወንጀለኛው መጥሪያ ለመስጠት ወይም የተፈፀመውን ወንጀል ለመመርመር የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ይርጋን የሚያቋርጡ ሲሆን እነዚህ ተከሳሹ ለፈፀመው የወንጀል ድርጊት ተገቢውን ፍርድ እንዲያገኝ ለማስቻል የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ሲቆሙ የይርጋ ዘመኑ እንደገና መቆጠር ይጀምራል። ሆኖም በተቋረጠ ቁጥር መቆጠር የሚጀምረው እንገና እንደ አዲስ ነው። ስለዚህም የይርጋ ጊዜው እንዲቋረጥ ያደረገው ምክንያት ከተከሰተበት ቀን በፊት ተቆጥር የነበረው የይርጋ ዘመን እንዳልነበረ ይቆጠራል።
2. የቅጣት የይርጋ ጊዜ
ከላይ እንደተገለፀው የቅጣት ይርጋ ቅጣት የተፈረደበት ሰው ቅጣቱ ተፈፃሚ ሳይሆንበት የተወሰነ ጊዜ ካለፈ ሊቀጣ እንደማይችል የሚደነግግ ነው። የቅጣት ይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚጀመረው በወንጀለኛው ላይ የተወሰነው ፍርድ ተፈፃሚ መሆን ይችል ከነበረበት፣ፍርድ መፈፀም ጀምሮ የነበረ እንደሆነ ተቀጪው ፍርድ እንዳይፈፀምበት ካመለጠበት ወይም ወንጀለኛው ፍርድ ታግዶለት የነበረ ከሆነና የማገድ ትዕዛዙ ተሽሮ ከሆነ የቅጣቱ አፈፃፀም እንዲቀጥል ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ከአንድ በላይ ቅጣት በወንጀለኛው ላይ ተወስኖበት ከሆነ የይርጋ ጊዜው የሚሰላው ከሁሉም ከባድ የሆነው ቅጣት የሚኖረው የይርጋ ጊዜ በመውሰድ ነው።

12/08/2025
12/08/2025

የሎተሪ ሥራ የህግ ሽፋን በኢትዮጵያ

መግቢያ
የሎተሪ ጨዋታ ከጥንት ማህበረሰብ ጀምሮ እንደመዝናኛ ወይም የእድል መሞከሪያ ሆኖ ጥቅም ላይ ሲውል የኖረ ነው። በተለይም በጥንታዊ ሥርዓቶች ውስጥ የነበሩ የንጉሳዊ ቤተሰቦች እንደ እጣፈንታ መወሰኛ ወይም በአንዳንድ ሁኔታዎች የኃይል ማሳያነት ሲጠቀሙበት የኖረ (የቆየ) የጨዋታ አይነት ነው። በአሁኑ ጊዜ ደግሞ የሎተሪ ንግድ እንደ አንድ የኢኮኖሚ ዘርፍ ተቆጥሮ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት በድንበር ተሻጋሪነትም (Site-Based) ሆነው ጭምር የሚሰሩት በኢንቨስትመንት ደረጃነት አድጓል። በኢትዮጵያ የሎተሪ እጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ገበያ ላይ የዋለው በ1954 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ-ሥላሴ ዘመን ነበር። ከዚህ ጊዜ በኋላ በቅርፅ፣ በሽልማት መጠንና በአደረጃጀት እያደገ መጥቶ በብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ስር በሚዘጋጁት ሎተሪዎች እንኳ በአሁኑ ሰዓት እስከ 50,000,000 (ሃምሳ ሚሊዮን) የሚደርስ የገንዘብ ሽልማት መጠን ያላቸው ሎተሪዎች በገበያ ላይ ይገኛሉ።

በተለይ አሁን አሁን ከቴክኖሎጅ እድገትና የዲጂታል ገበያው መስፋት ጋር በተያያዘ የሎተሪ አጨዋወቱ ዘዴም በፍጥነት በመዘመን ላይ የሚገኝ ሲሆን ለምሳሌም አንዳንድ ድርጅቶች ከአካላዊ ውርርድ እስከ አጭር የፅሁፍ መልዕክት፣ ዌብሳይት፣ መተግበሪያዎችና መሰል ዘዴዎችን በመጠቀም የሎተሪ እጣዎችን የሚሸጡበት ወይንም ውርርዶችን የሚያካሂዱበትን ሁኔታ እናስተውላለን። በዚህ አጭር ፅሁፍ ስለሎተሪና ውርርዶች ምንነት፣ የህግ መሠረት፣ የአሰራር ቅድመ ሁኔታዎችና መስፈርቱን አሟልቶ አለመስራት ሊያስከትል ስለሚችለው የህግ ተጠያቂነት ተዳሷል።

ሎተሪ ምንድነው ?
ሎተሪ ቃሉ የእንግሊዝኛ ሲሆን በሀገራችንም እንዳለ ተወስዶ ለቃሉ የህግና የመዝገበ-ቃላት ፍች ተሰጥቶት እናገኛለን። ለዚህም እንደምሳሌ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናት ኢንስቲትዩት ያሳተመው የአማርኛ መዝገበ ቃላት “ሎተሪ የሚለውን ቃል “ተከታታይ ቁጥሮች የተሰጧቸው ብዙ ትኬቶች ለሰዎች ከተሸጡ በኋላ እጣ በመጣል አሸናፊ ለሆነው ቁጥር የተወሰነለትን ገንዘብ… እቃ በመስጠት የሚካሄድ ተግባር ነው” የሚል ፍች ሰጥቶታል። በሌላ በኩል የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደርን እንደገና ለማቋቋም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው ደንብ ቁጥር 160/2001 አንቀፅ 2(1) መሠረት “ሎተሪ” ማለት የሽልማት አሸናፊው በእድል በእጣ አወጣጥ ወይም በማንኛውም ሌላ ዘዴ የሚታወቅበት ጨዋታ ወይም ድርጊት ሲሆን ቶምቦላን ወይም ራፍልን፣ ሎቶን፣ ቶቶን፣ ፈጣን ሎተሪን፣ የቁጥር ሎተሪን የተደራራቢ ሽልማት ሎተሪን፣ የፕሮሞሽን ሎተሪን፣ ቢንጎን፣ የስፖርት ውርርድ ሎተሪንና ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችን ይጨምራል። በአጠቃላይ ደንቡ ከመውጣቱ በፊት በስራ ላይ በነበረው አዋጅ ቁጥር 535/1999 ስር ተካተው የነበሩ ከአስር በላይ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የሎተሪ አይነቶችን ከነትርጓሜያቸው እንዲቀጥሉ አድርጓል። በዚህም አሁን ላይ አንዳንዶችን በሁለት ጎራ ከፍሎ የሚያከራክረውን የስፖርት ውርርድ (ለጊዜው በአዲስ አበባ ደረጃ የተከለከለ) ጨምሮ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት፣ በመተግበሪያዎችና በዌብ ሥርዓት የሚደረጉትን እንዲሁም ወደፊት ሊጨመሩ የሚችሉ መሰል የእጣ ውርርዶችን ሊጨምር የሚችል ሰፊ ትርጓሜ ነው።

በሎተሪ ሥራ ለመሰማራት መሟላት ያለባቸው ቅድመ-ሁኔታዎች
በደንቡ አንቀፅ 2(13) ስር የሎተሪ ሥራ ምንነትን አስመልክቶ የተቀመጠውን ትርጓሜ ስንመለከት፣ የሎተሪ ስራ ማለት ‘በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ማንኛውንም ሎተሪ በማዘጋጀት በሀገር ውስጥ መሸጥ፣ ማከፋፈል፣ ማጫወትና እጣ ማውጣት ወይም ሌላ ተመሳሳይ ተግባራት ማከናወን ነው በሚል ሰፍሯል። በዚህ መሠረት ማንኛውም አካል፣ ግለሰብ ይሁን ድርጅት እነዚህን በመሰሉ የሎተሪ ሥራ ተግባራት ላይ ለመሰማራት በዚህ ደንብ አንቀፅ 12 ጀምሮ በዝርዝር የሰፈሩትን ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላትና ማክበር እንዳለበት ተመላክቷል። ከእነዚህ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታዎች መካከልም፣-
 የሎተሪ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር የተሰጠ የፀና ፈቃድ፣
 በሎተሪ ሥራ ለመሰማራት በአዋጁ በግለሰብ ወይንም ከመንግስት ጋራ በጣምራ ሊሰራ የሚችል መሆኑን መለየት፣
 ተገቢ ክልከላዎችን ማክበር፣ (ዝቅ ብሎ እንደተመላከተው)
 ፈቃዱ የህዝብን ሠላምና ፀጥታ ወይም የሀገሪቱን ደህንነት የሚጎዳ የወንጀል ተግባር ላይ እንዳይውል የማድረግ ግዴታ
 እንዲሁም በወንጀል አስቀጭ ተብለው ከተዘረዘሩ ተግባራት በመቆጠብ የሎተሪ ሥራን በህጋዊ መንገድ ማካሄድ የሚሉት ይገኙበታል።
ከዚህ ጋር በተያያዘም በደንቡ አንቀፅ 2(5፣6፣7፣8፣9 እና 110) ስር የሰፈሩት ማለትም፣-ቶቶ፣ ፈጣን ሎተሪ፣ የቁጥር ሎተሪ፣ የተደራራቢ ሽልማት ሎተሪ እና ዘመናዊ የቢንጎ ሎተሪን በአስተዳደሩ ብቻ የሚካሄዱ በመሆናቸው ምክንያት ግለሰብ ወይም የግል ድርጅት በእነዚህ የሎተሪ ተግባራት ላይ መሰማራት አይችልም። በሌላ መልኩ በአንቀፅ 2(3፣4፣19 እና 12) ስር የተካተቱት ማለትም የቶምቦላ ወይም ራፍል ሎተሪ፣ የስፖርት ውርርድ ሎተሪ፣ ኮንቬንሽናል ቢንጎና የፕሮሞሽን ሎተሪ በማንኛውም ሰው ሊሰሩ የሚችሉ ናቸው። ከዚህ ሌላ በተለይ የቶቶና ፈጣን ሎተሪዎችን አስተዳደሩ አስፈላጊው ካፒታል፣ ቴክኖሎጂና የእውቀት አመራር ያላቸው የግል ተሳታፊዎች ጋር በጋራ ሽርክና ሊሰራቸው የሚችሉ ስለመሆናቸው ተመላክቷል።
ከዚህ ባለፈ ደንቡ በአንቀፅ 17 ስር ውስን ክልከላዎችን ያስቀመጠ ሲሆን በዚህም፣- ማንኛውም ሰው ከአስተዳደሩ የተሰጠ ፈቃድ ሳይኖረው ማንኛውንም የሎተሪ ሥራ ማካሄድ አይቻልም፣ በተጨማሪም ማንኛውም ሰው የሎተሪ ሥራ ለማካሄድ የተሰጠውን ፈቃድ ያለአስተዳደሩ ስምምነት ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠት

የተከለከለ ተግባር መሆኑ ተደንግጓል።
ክልከላዎችን መተላለፍና የወንጀል ተጠያቂነት
በደንቡ አንቀፅ 20 ስር ግልፅ የወንጀል ክልከላዎች የተቀመጡ ሲሆን በዚህም በወንጀል ህጉ ከፍ ያለ ቅጣት ከሌለ በቀር ማንኛውም ሰው የፀና ፈቃድ ሳይኖረው የሎተሪ ስራ ያካሄደ እንደሆነ ከሃምሳ እስከ መቶ ሽህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እና ከሦስት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል። እንዲሁም ማንም ሰው የህንፃ ይዞታውን ለህገ-ወጥ የሎተሪ መሸጫ እንዲውል ያከራየ ወይም በማንኛውም ሁኔታ የተፈቀደ ወይም በአስተዳደሩ ለቁጥጥር የተላከን ሰራተኛ እንዳይገባ የከለከለ ወይም የቁጥጥር ሥራው እንዳይካሄድ በማንኛውም መንገድ ያሰናከለ ከብር አስር ሺህ እስከ ሃያ ሺህ ብር መቀጮ እና ከአንድ ዓመት እስከ ሁለት ዓመት በሚደርስ የእስር ቅጣት ይቀጣል።

ከእነዚህ በዝርዝር ከሰፈሩት የሚያስቀጡ ተግባራት በተጨማሪ እንደተፈፀመው ድርጊት ሁኔታ የወንጀል ህጉ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ። በዚህም ምሳሌ በአንቀፅ 692 ስር አታላይነትን አስመልክቶ የሚከተለው ሰፍሯል፣-
ማንም ሰው የማይገባ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ አሳሳች የሆኑ ነገሮችን በመናገር የራሱን ማንነት ወይም ሁኔታ በመሰወር፣ ወይም መግለፅ የሚገባውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት ወይም ግምት በመጠቀም ፣ በማድረግ ሆነ ባለማድረግ ሌላውን ሰው አታሎ የራሱን ወይም የሦስተኛ ወገን የንብረት ጥቅም የሚጎዳ አድራጎት እንዲፈፀም ያደረገ እንደሆነ በቀላል እስራት ወይም እንደነገሩ ከባድነት ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራትና በመቀጮ እንደሚቀጣ ተደንግጓል።

በመጨረሻም ምንም እንኳ በዚህ ፅሁፍ የተሸፈነውን አዋጅ ቁጥር 535/1999 በግልፅ ባይሽረውም በ2001 ዓ.ም በይዘት ከአዋጁ ብዙም ያልተለየ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደርን ለማቋቋም የወጣ ደንብ ቁጥር 160/2001 በሥራ ላይ ይገኛል። ደንቡ በአዋጁ ከተካተቱት የወንጀል ቅጣቶች በተጨማሪ ዝርዝር አስተዳደራዊ ቅጣቶችን ያካተተ ሲሆን በተለይም በሐሰተኛና በተጭበረበረ ማስረጃ የተገኘ ፈቃድ ሲሆን፣ ፈቃዱ የህዝብን ሰላምና ፀጥታ ወይም የሀገሪቱን ደህንነት የሚጎዳ የወንጀል ተግባር ሲሰራበት፣ በተሰጠው የጊዜ ገደብ (በየበጀት አመቱ) ያላሳደሰ እንደሆነ እንደሁኔታው ከማገድ እስከ ፈቃድ ስረዛ የሚደርስ እርምጃ ለመውሰድ ይችላል።

ማጠቃለያ
የሎተሪ ጨዋታ ራሱን የቻለ በእድል ጨዋታ የተመሰረተ የስራ ዘርፍ (Gaming Profession) ነው። ይሁን እንጂ በዚህ ሥራ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች አሁን በስራ ላይ ባለው የንግድ ህግ በተለይም አንቀፅ 5 ስር እንደተመላከተው ነጋዴ ሊባሉ የሚችሉ ስላልሆኑ የንግድ ፈቃድ ምዝገባ ማድረግ አይጠበቅባቸውም። በአንፃሩ ከፍ ብሎ እንደተብራራው በሎተሪ ሥራ ውስጥ የሚሰማራ ማንኛውም ሰው ግንኙነቱ የሚመራው በደንቡና እሱን ተከትለው በሚወጡ መመሪያዎች መሰረት ሆኖ ግንኙነቱም በዚሁ ደንብ ከተቋቋመው የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ጋር ይሆናል።
ሌላው በዚህ ፅሁፍ ሽፋን የተሰጠው የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደርን እንደገና ለማቋቋም የወጣው ደንብ ቁጥር 160/2001 ሲሆን ነገር ግን ደንቡ በተለይ በአንቀፅ 20 ላይ የደነገጋቸው የወንጀል ቅጣቶች ከደንቡ በፊት በሥራ ላይ ከነበረው አዋጅ 535/1999 በቀጥታ የመጡ እንደሆኑና በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 55(5) በሰፈረው መሠረት የወንጀል ህግ የሚወጣው በፌደራሉ የህግ አውጭ ምክር ቤት ብቻ በመሆኑ የወንጀል ቅጣት የያዘው የአዋጁ ድንጋጌ ያልተሻረ ስለመሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።

በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገጽን ይቀላቀሉ
Website
https://www.justice.gov.et
Facebook
https://www.facebook.com/MOJEthiopia/
(x) Twitter
https://x.com/MOJEthiopia
YouTube channel
https://youtube.com/...3701 ...
LinkedIn
https://www.linkedin.com/.../ministry-of-justice.../about/
Telegram
https://t.me/fdreattorneyGeneral_externa

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች          ክፍል 1 ========================በወንጀል ጉዳይ የግል አቤቱታ ወይም ክስ የማቅረብ እና ጉዳዩን በዳኝነት የማየት እንዲሁም ቅጣትን ተፈጻሚ...
12/08/2025

ይርጋ በወንጀል ጉዳዮች
ክፍል 1
========================
በወንጀል ጉዳይ የግል አቤቱታ ወይም ክስ የማቅረብ እና ጉዳዩን በዳኝነት የማየት እንዲሁም ቅጣትን ተፈጻሚ እንዲሆን የማድረግ እንቅስቃሴዎች በጊዜ የተገደቡ ናቸው፡፡ ይህ የጊዜ ገደብ እንደ ወንጀሉ ከባድነት የሚለያይ ሲሆን “ይርጋ” ተብሎ ይጠራል፡፡ የክስ ይርጋ የወንጀል ድርጊት ፈጽሟል ተብሎ የተጠረጠረ ሰው የወንጀል ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በዳኝነት ሳይታይ የተወሰነ ጊዜ ካለፈ ሊከሰስ የማይችል ስለመሆኑ የሚደነግግ ሲሆን የቅጣት ይርጋ ደግሞ ቅጣት የተፈረደበት ሰው ቅጣቱ ተፈፃሚ ሳይሆንበት የተወሠነ ጊዜ ካለፈ ሊቀጣ እንደማይችል የሚደነግግ ነው፡፡

ይርጋ የወንጀል ክስም ሆነ ቅጣት ቀሪ እንዲሆኑ የማድረግ ውጤት ቢኖረውም በአንዳንድ የወንጀል ጉዳዮች ዙሪያ እንዲህ ዓይነት አሰራሮችን በመከተል ወንጀል አድራጊዎች ከቅጣት እንዲያመልጡ ማድረግ በሕብረተሰቡ መብትና ጥቅም ላይ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ይታመናል፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንድ የወንጀል ዓይነቶች ይርጋ አይኖራቸውም፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ሕገ መንግስት አንቀጽ 28 ላይ እንደተደነገገው በስብዕና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በይርጋ አይታገዱም፡፡ ይህን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ ግምት ውስጥ በማስገባትም በስብዕና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በይርጋ ቀሪ ሊሆኑ እንደማይችሉ ለማመልከት “በሕግ በሌላ አኳኋን በግልፅ ካልተደነገገ በስተቀር” የሚል ሀረግ በአዲሱ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 216 እና 223 ስር እንዲገባ ተደርጓል፡፡

1. #የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ጊዜ

ከዚህ በላይ እንደተጠቀሰው የክስ ይርጋ የወንጀል ድርጊት ፈጽሟል ተብሎ የተጠረጠረ ሰው የወንጀል ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በዳኝነት ሳይታይ የተወሰነ ጊዜ ካለፈ ሊከሰስ የማይችል ስለመሆኑ የሚደነግግ ሲሆን የይርጋ ጊዜው መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡ ሆኖም ወንጀሉ በተለያዩ ጊዜያት የተፈፀመ ከሆነ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ሲሆን ወንጀሉ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆዬ ከሆነ ደግሞ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ መፈፀም ካቆመበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡

የይርጋ ዘመን የሚቆጠረው የቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ ምክንያቶች ግምት ውስጥ ሳይገቡ ለተፈፀመው ወንጀል በሕጉ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሰረት በማድረግ ነው፡፡ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈፅመው በሚገኙበት ጊዜ የክስ ማቅረቢያው ጊዜ የሚወሰነው የተደራራቢዎች ወንጀሎች የቅጣት ጣራ ተመሳሳይ ከሆነ የአንደኛው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ ዘመን ለሌሎቹ ወንጀሎች ተፈፃሚ የሚደረግ ሲሆን የተደራራቢዎቹ ወንጀሎች ቅጣት ጣራ የተለያዬ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ የከባዱ ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ በዚህም መሠረት የአንዱ ተመሳሳይ ወንጀል ወይም ከተደራራቢ ወንጀሎች ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በሌሎቹ ተደራራቢ ወንጀሎች ምክንያት የይርጋ ጊዜው እንዲራዘም አይደረግም ማለት ነው፡፡ የወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ተከሣሹ ተደራራቢ ወንጀሎችን ፈፅሞ ከሆነ የይርጋ ጊዜው የሚወሰነው እንዴት እንደሆነ አይደነግግም ነበር፡፡

የይርጋ ዘመን መቆጠር ከጀመረ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ሊታገድ ወይም ሊቋረጥ ይችላል፡፡ ከወንጀለኛው ድርጊት ሌላ ክስ እንዳይቀርብ ወይም እንዳይቀጥል የሚያደርጉ መሰናክሎች ሲከሰቱ የይርጋ ዘመን መቆጠር ይታገዳል፡፡ እነዚህ መሰናክሎች የህግ ወይም የፍሬ ነገር (የሁኔታ) መሰናክሎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Address

Konta Zone
Ameya

Telephone

+251472270002

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኮንታ ዞን ፍትህ መምሪያ/Konta Zone Justice Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share