30/04/2026
የፓርቲው ጥንካሬና ጤናማነት የሚወሰነው በኢንስፔክሽን ስራ ለውጤታማነት በትኩረት እንደሚገባ ተገለጸ
=====
ሚያዚያ 21/2018 የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግመዋል።
በአፈጻጸም ግምገማ ላይ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ሀሰን እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ደግሞ የኢንስፔክሽን ስራ የላቀ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
የፓርቲው ጥንካሬና ቀጣይነት የሚወሰነው በኢንስፔክሽን ስራው ጥራት መሆኑን ሰብሳቢው አቶ መሀመድ ሀሰን ገልጸዋል።
የአመራሩና የአባላቱ ስነ-ምግባር፣ የፓርቲው ሀብትና ንብረት በአግባቡ መጠበቁን ማረጋገጥ የኮሚሽኑ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአፈጻጸሙ የታዩ ጉድለቶች ለቀጣይ እርማት ተውስዶበት ጠንካራ ጎን እንድቀጥል ኮሚሽን ኮሚቴው አባላት ታችኛው መዋቅር በትኩረት መስራት እንደሚ አሳስበዋል።
ብልፅግና የማረጋገጥ ጉዟችን እንዲሳካ በፓርቲው የአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ስህተቶችን የማረም ሀላፊነቱን ለመወጣት ኮሚሽኑ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በበየጊዜው የሚያከናውናቸውን ጠንካራ የኢንስፔክሽን ስራዎች ግኝት ለፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በማቅረብ ተፈፃሚነታቸውን በመከታተል ለላቀ ድል አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ኢንጂነር መዲና አለሙ በበኩላቸው በየግዜው የሚሰራቸው ስራዎች ግምገማ ማድረግ የፓርቲውን ውስጣዊ አሰራርና አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።
የኮሚሽኑ አመራሮች ሀብትና ንብረትን ከመቆጣጠር አንፃርና ብልሹ አሰራሮችን በመታገል እየመጡ ያሉ ለውጦችን ማስቀጠል የሁሉ ድርሻ ሊሆን ይገባልም ብለዋል።
ተቋማዊ ግንባታን በማስቀደም አደረጃጀቶችን ማጠናከርና በግንባር ቀደሞች እንዲመሩ ማድረግ ትኩረት እንዲሰጠው ጠቁመዋል።
አክለውም መድረኩ ጠንካራ ጎኖችን የምናጠናክርበትና ያሉብንን ደካማ ጎኖች በመለየት በቀጣይ ለምናከናውነው ተግባር መሠረት የምንጥልበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ፓርቲው ለሚያካሂደው ምርጫ ስኬታማነት የኢንስፔክሽን ዘርፉ የራሱን አሻራ እያሳረፈ እንደሚገኝ ጠቁመው ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊና አካታች እንዲሆን የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
በተለይም ከመደበኛ ስራ ጎን ለጎን እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የምርጫ ዝግጅቶች በከፍተኛ ኃላፊነት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሌላው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በስነ-ምግባርና በቅሬታ አፈታት ዙሪያ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም ዘርፎች ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።
የሶስቱም ወረዳዎች እና የከተማ አስተዳደር ኮሚሽን ስራ አመራሮች ባለፉት 9 ወራት በዘርፉ በየደረጃው የተሰሩ ስራዎች ቀርበው በሰፊው ተገምግመው የቀጣይ ስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የዞኑ መንግሥት ኮሙ