የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Alaba K'ulito
  • የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት ይህ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት የፌስቡክ ገጽ ነው ።

የፓርቲው ጥንካሬና ጤናማነት የሚወሰነው በኢንስፔክሽን ስራ ለውጤታማነት በትኩረት እንደሚገባ ተገለጸ =====ሚያዚያ 21/2018 የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽ...
30/04/2026

የፓርቲው ጥንካሬና ጤናማነት የሚወሰነው በኢንስፔክሽን ስራ ለውጤታማነት በትኩረት እንደሚገባ ተገለጸ
=====

ሚያዚያ 21/2018 የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግመዋል።

በአፈጻጸም ግምገማ ላይ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ሀሰን እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ደግሞ የኢንስፔክሽን ስራ የላቀ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የፓርቲው ጥንካሬና ቀጣይነት የሚወሰነው በኢንስፔክሽን ስራው ጥራት መሆኑን ሰብሳቢው አቶ መሀመድ ሀሰን ገልጸዋል።

የአመራሩና የአባላቱ ስነ-ምግባር፣ የፓርቲው ሀብትና ንብረት በአግባቡ መጠበቁን ማረጋገጥ የኮሚሽኑ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአፈጻጸሙ የታዩ ጉድለቶች ለቀጣይ እርማት ተውስዶበት ጠንካራ ጎን እንድቀጥል ኮሚሽን ኮሚቴው አባላት ታችኛው መዋቅር በትኩረት መስራት እንደሚ አሳስበዋል።

ብልፅግና የማረጋገጥ ጉዟችን እንዲሳካ በፓርቲው የአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ስህተቶችን የማረም ሀላፊነቱን ለመወጣት ኮሚሽኑ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በበየጊዜው የሚያከናውናቸውን ጠንካራ የኢንስፔክሽን ስራዎች ግኝት ለፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በማቅረብ ተፈፃሚነታቸውን በመከታተል ለላቀ ድል አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ኢንጂነር መዲና አለሙ በበኩላቸው በየግዜው የሚሰራቸው ስራዎች ግምገማ ማድረግ የፓርቲውን ውስጣዊ አሰራርና አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

የኮሚሽኑ አመራሮች ሀብትና ንብረትን ከመቆጣጠር አንፃርና ብልሹ አሰራሮችን በመታገል እየመጡ ያሉ ለውጦችን ማስቀጠል የሁሉ ድርሻ ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

ተቋማዊ ግንባታን በማስቀደም አደረጃጀቶችን ማጠናከርና በግንባር ቀደሞች እንዲመሩ ማድረግ ትኩረት እንዲሰጠው ጠቁመዋል።

‎አክለውም መድረኩ ጠንካራ ጎኖችን የምናጠናክርበትና ያሉብንን ደካማ ጎኖች በመለየት በቀጣይ ለምናከናውነው ተግባር መሠረት የምንጥልበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ፓርቲው ለሚያካሂደው ምርጫ ስኬታማነት የኢንስፔክሽን ዘርፉ የራሱን አሻራ እያሳረፈ እንደሚገኝ ጠቁመው ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊና አካታች እንዲሆን የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በተለይም ከመደበኛ ስራ ጎን ለጎን እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የምርጫ ዝግጅቶች በከፍተኛ ኃላፊነት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።

ሌላው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በስነ-ምግባርና በቅሬታ አፈታት ዙሪያ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም ዘርፎች ስራዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።

የሶስቱም ወረዳዎች እና የከተማ አስተዳደር ኮሚሽን ስራ አመራሮች ባለፉት 9 ወራት በዘርፉ በየደረጃው የተሰሩ ስራዎች ቀርበው በሰፊው ተገምግመው የቀጣይ ስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የዞኑ መንግሥት ኮሙ

በለውጡ መንግስት የተመዘገቡ ስኬቶችን ማስፋት እና ማላቅ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሆሳዕና፣ሚያዚያ 19/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክል...
27/04/2026

በለውጡ መንግስት የተመዘገቡ ስኬቶችን ማስፋት እና ማላቅ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ሚያዚያ 19/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወራቤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በድጋፍ ሰልፉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት በለውጡ መንግስት የተመዘገቡ ስኬቶችን ማስፋት እና ማላቅ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው ብለዋል።

የፖለቲካ ኢኮኖሚ የስርዓት ቅኝት ለአንዲት ሀገር እጣ ፈንታ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታ ነው ብለዋል።

የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስርዓት ቅኝታቸውን ከሀገራዊ ነባራዊ አውድ ጋር በተስማማባቸው ሀገራት ፈጣን እና ተከታታይነት ያለው የእድገት እንዲመዘገብ ያስችላል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

ይህ የለውጥ እና የእድገት ቅድመ ሁኔታ ባልተሳካባቸው ሀገራት ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ አዳጋች ይሆናል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

የፖለቲካ ኢኮኖሚ ስርዓት ቅኝት እና የቅኝቱ አዳጊ ሽግግር በሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ቅቡልነት ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያን ለውጥ ማሳለጥ የሚችሉ እና በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ የተቃኙ የፖለቲካ ስርዓቶች አለመገንባታቸው የሀገራችንን እድገት ጎድቷል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበው የፖለቲካ ስርዓት ሽግግር በሚፈለገው ደረጃ የህዝብ ተጠቃሚነትን ሳያረጋግጥ መቆየቱን ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል።

አዲሱን ሀገራዊ ለውጥ ተከትሎ ከመደመር እሳቤ የተቀዳው መንግስት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ኢኮኖሚ ስርዓት መሰረት አድርጎ በመንቀሳቀስ ቀደም ሲል ሲያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን ማረም እንዳስቻለም ጠቁመዋል።

ለሁለንተናዊ ብልጽግና ምቹ መደላድል እየፈጠሩ የሚገኙ ታላላቅ ስኬቶች እንዲመዘገቡ መሰረት መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

ሀገራዊ ለውጡ ወረቶችን በማስቀጠል ፣ቁርሾዎችን እና የጥላቻ ምዕራፎችን በመዝጋት ለመጪው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ምቹ መደላድል ስለመፈጠሩም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

በመደመር እሳቤ የተመሩ የሪፎርም ማሻሻያ እርምጃዎችን ተግባራዊ በማድረግ አዳዲስ የለውጥ እንቅስቃሴዎች መደረጋቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት አመላክተዋል።

በፖለቲካዊ ፣በማህበራዊ ፣በኢኮኖሚያዊ እና በዲፕሎማሲ መስኮች ዘርፈ ብዙ ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በተደረገው ጥረት ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መደላድል የሚፈጥሩ ታላላቅ የለውጥ እርምጃዎች ስለመወሰዳቸውም አብራርተዋል።

በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ መግባባት እንዲቻል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በሀገር በቀል የኢኮኖሚ በመታገዝ ያሉትን ጸጋዎች እና ልዩ ልዩ አቅሞችን በመጠቀም በተከናወኑ ስራዎች አስደማሚ ውጤት ተመዝግቧል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የቱሪዝም አማራጮቻችን ወደ ኢኮኖሚ ዋልታነት እየተሸጋገሩ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

በቴክኖሎጂም መስክ ዘመኑን ሊመጥኑ የሚችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና የኢንስፔክሽንና የስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ከዞን እና ከልዩ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤቶች ጋር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ የአሰራር ስረዓት መመሪያ አፈጻጸምን ...
17/04/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና የኢንስፔክሽንና የስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ከዞን እና ከልዩ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤቶች ጋር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ የአሰራር ስረዓት መመሪያ አፈጻጸምን እንዲሁም ወቅታዊ ተግባራትን አስመልክቶ በበየነ መረብ ግምገማ አካሄደ።

07/08/2018 ዓ.ም ሆሳዕና

በግምገማዉ የኢንስፔክሽንና የሥነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል እንደገለጹት የፓርቲዉ የምርጫ የአሰራር ስረዓት መመሪያ ተፈጻሚነት በየደረጃዉ በሚገኙ የኮሚሽን መዋቅሮች የክትትል ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

አክለዉም 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ብልጽግና ፓርቲ የምርጫ የአሰራር ስረዓት መመሪያ በማውጣት ለፓርቲው አባላትና አመራሮች ግንዛቤ በመፍጠር መመሪያው በጥብቅ ዲስፒሊን ተግባራዊ እንድደረግ በጽኑ እየሰረ መሆኑን በመጥቀስ በየደረጃው ያለው ኮሚሽን ፓርቲው ያስቀመጣቸው ግቦች እንዲሳኩ በፓርቲው የምርጫ የአሰራር ስረዓት መመሪያ ለኮሚሽኑ የተሰጠውን ሚና በተገቢው ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽን እና ሥነምግባር ኮሚሽን ቅ/ቤት ም/ኃላፊ ወ/ሮ ሂሩት ተሾመ በበኩላቸዉ እድሜው ለመራጭነት የደረሰ የክልላችን ነዋሪዎች በሙሉ ለመራጭነት የሚያበቃዉን የምርጫ ካርድ በቀሩት ዉስን ቀናቶች መዉሰድ እንዲችሉ ለነዋሪዎች መረጃ የመስጠት የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት በመሆኑ ተጠናክሮ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም በቀጣይ ሶስት ቀሪ ወራቶች ያልተጠናቀቁ የኮሚሽኑን ተግባራት በመለየት በልዩ ትኩረት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጋራ በማድረግ የነበረው የተግባራት አፈጻጸም የግምገማ መድረክ ተጠናቆዋል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚዲያ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።‎‎ የኢትዮጵያ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ  ዙሪያ በሀላባ በዞን በሚገኙ ከሚዲያ አካለት ጋር ዉይይት መድረክ ተካ...
11/04/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚዲያ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

‎ የኢትዮጵያ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ በሀላባ በዞን በሚገኙ ከሚዲያ አካለት ጋር ዉይይት መድረክ ተካሄደዋል ።

‎ለመድረኩ የተዘጋጀው ስነድ የሀላባ ዞን ብ/ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ሀላፊ አቶ በድሩ ከድር አቅርቧል።
‎​
‎​ የሀላባ ዞን ብ/ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ሀላፊ አቶ በድሩ ከድር እንደተናገሩት ​ሚዲያዎች ለማህበረሰቡ ትክክለኛ፣ ሚዛናዊና ወቅታዊ መረጃዎችን በማቅረብ ህዝቡ በንቃት በምርጫው እንዲሳተፍ የማንቃት ስራ መስራት እንዳለባቸው ገልጿል።

‎​አክለውም ምርጫውን ተገን በማድረግ ግጭት ቀስቃሽ ንግግሮችና የሐሰተኛ መረጃዎች (Fake News) ስርጭትን በመከላከል ረገድ ሚዲያው እንደ ጠባቂ ሊሰራ እንደሚገባ በአጽንኦት አስገንዝበዋል ።

‎​መራጮች ስለ መብትና ግዴታቸው፣ ስለ ምርጫ ስነ-ምግባርና ስለ ድምፅ አሰጣጥ ሂደት በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የማድረግ ስራ የሚዲያ አካላት ቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበት ተጠቁሟል።

‎​አቶ በድሩ ከድር ሚዲያ የዴሞክራሲ የጀርባ አጥንት ነው፤ በመሆኑም 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጥ እንዲሆን የሚዲያ ባለሙያዎች በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብሏል ።

‎7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና በስኬት እንዲጠናቀቅ የሚዲያ አካላትና የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ሚና የማይተካ መሆኑን የሀላባ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀሩና አህመድ ገልጿል ።

‎​የመምሪያው ኃላፊ አቶ ሀሩና አህመድ እንደገለጹት፣ ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ዋነኛ አካል በመሆኑ፣ ሂደቱ ግልጽነት የሰፈነበትና ህዝባዊ አመኔታ ያገኘ እንዲሆን ሚዲያዎች በሃላፊነት ሊሰሩ ይገባል ብሏል።

‎ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት በሚዲያ አማካኝነት በሚፈጠር ግልጽነትና ህዝባዊ ንቅናቄ ጭምር ነው። የሚዲያ አካላት በነፃነትና በሃላፊነት ስሜት የሚሰሩት ስራ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሰረት መሰረት መሆኑን ሀላፊው ገልጿል ።

‎በተጨማሪም በምርጫ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱ የሐሰት ወሬዎች በህዝብ ደህንነትና በምርጫው ተአማኒነት ለማበላሸት የሚፈልጉ ፣አካላት በጽኑ መታገል እና መረጃን ከምንጩ በማጣራት (Fact-checking) ረገድ ግንባር ቀደም መሆን አለባቸው ብሏል ።

‎የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ሙያዊ ስነ-ምግባርን በመጠበቅ፣ ከወገንተኝነት የፀዳና ለሀገር ግንባታ ቅድሚያ የሚሰጥ ዘገባ ማቅረብ እንዳለባቸው አቶ ሀሩና አሳስበዋል።

‎በቀረበው ስነድ ዙሪያ ሰፈ ያለ ዉይይት ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቀዋል ።

‎በመድረኩ ላይም የሀላባ ዞን የሚዲያ አመራሮች የመዋቅር የሚዲያ አመራሮች የዞኑ የሚዲያ ፎካሎች ተገኝተዋል ።

‎ሲል የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽህፈት ቤት ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ዘግቧል
‎ወቅታዊ፣ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎችን ለመግኘት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ሊንክ ይጫኑና ይውደዱ!፣ይከታተላሉን!!.

‎1.✍ ዌብሳይት=https://www.halaba.gov.et/ halaba_zone_prosperity_party/
‎2.✍ ፌስቡክ ገጽ/ፔጅ ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100086848601712
‎3.✍ https://www.tiktok.com/?_t=8Y68uIjujdF&_r=1
‎4.✍ ትዊተር አካውንት ፣
https://mobile.twitter.com/HalabaPP()
‎5.✍ ቴሌግራም ቻነል

የኢፌዴሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ሒክማ ኸይረዲን እና የኢፌዴሪ የስራና ክህሎት ሚንስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድናስር በዌራ ዲጆ ወረዳ በሀላባ ምርጫ ክልል ቁ.1 ለ...
11/04/2026

የኢፌዴሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ሒክማ ኸይረዲን እና የኢፌዴሪ የስራና ክህሎት ሚንስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድናስር በዌራ ዲጆ ወረዳ በሀላባ ምርጫ ክልል ቁ.1 ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ለማድረግ በበሸኖ ቀበሌ ኮልሚኔ ትምህርት ቤት ምርጫ ጣቢያ የምርጫ ካርድ ወሰዱ።

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል።

በዚህም በዛሬው ዕለት የኢፌዴሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ሒክማ ኸይረዲን፣የስራና ክህሎት ሚንስቴር ዴዕታ ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድናስር በዌራ ዲጆ ወረዳ በሀላባ ምርጫ ክልል ቁ.1 ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በበሸኖ ቀበሌ ኮልሚኔ ትምህርት ቤት ምርጫ ጣቢያ የምርጫ ካርዳቸውን ወስደዋል።
ምንጭ ሀላባ ቲቪ!

በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩዎችን የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር መድረክ ተካሄደ ሚያዝያ 1/2018 ብልፅግና ...
10/04/2026

በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩዎችን የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር መድረክ ተካሄደ

ሚያዝያ 1/2018 ብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ የሀላባ ዞንን በመወከል ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እና ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ እጩዎችን የማስተዋወቂያ መድረክ ተካሄደዋል።

በመርሃ ግብሩ በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር የሚወዳደሩ ዕጩዎች ቀርበው ለአባላቱ ተዋዉቀዋል።በዚህም መሰረት፦

➡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፦✍ክብርት ዶክተር ነጃት ግርማ የፓርላማ አባል፣

➡ ለክልል ምክር ቤት፦✍ ክብርት ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ፣
✍.ዶክተር መሀመድ ኑርዬ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ-ልማት አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ፣
✍ ክብርት መነቴ ሙንዲኖ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ፣
✍ ክብርት ወ/ሮ በይዳ ሙንዲኖ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ፣
✍ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣
✍ክቡር አቶ መሀመድከማል ኑርዬ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የዞኑ ዋና የመንግሥት ተጠሪ፣
✍ ገረድ ድልታታ ሙዜ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አባል፣

በመድረኩ የፌዴራል፣የክልልና ዞን ማዕከል፣የወረዳ እና ከተማ የፓርቲና መንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል።

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት
ወቅታዊ፣ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎችን ለመግኘት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ሊንክ ይጫኑና ይውደዱ!፣ይከታተላሉን!!.

1.✍ ዌብሳይት=https://www.halaba.gov.et/ halaba_zone_prosperity_party/
2.✍ ፌስቡክ ገጽ/ፔጅ ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100086848601712
3.✍ https://www.tiktok.com/?_t=8Y68uIjujdF&_r=1
4.✍ ትዊተር አካውንት ፣
https://mobile.twitter.com/HalabaPP()
5.✍ ቴሌግራም ቻነል፦
https://t.me/halabazoneprosperityparty
6.✍ ዩቲዩብ ቻነል፦ https://youtube.com/channel/UCNo-vCe1fj6b6z2rLitKAUA
7.✍ LinkedIn ፦
www.linkedin.com/in/halaba-zone-1a1235241
8.✍ ኢንስታግራም፦
http፡//www.Instagram.com/tv/ CWMLYs2lwop/?utm-medium" ፣
9.✍https://whatsapp.com/channel/0029VavGrJv4dTnS81aPuy3O

የብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን እኩልነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ስሰራ ቆይቷል፦አቶ ራመቶ ሙሀመድ ******ሚያዝያ፣1/2018 በሀላባ ዞን  የብልጽግና ፓርቲ ለሴቶች ክንፍ አመራሮ...
09/04/2026

የብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን እኩልነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ስሰራ ቆይቷል፦አቶ ራመቶ ሙሀመድ
******
ሚያዝያ፣1/2018 በሀላባ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ለሴቶች ክንፍ አመራሮችና አባላት ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የመወዳደሪያ ማንፌስቶ ( የመወዳደሪያ ምልክት)የሆነውን የስንዴ ነዶን የማስተዋወቅ መርሐግብር በቁሊቶ ከተማ ተካሄዷል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ራመቶ ሙሀመድ በዚሁ መርሐግብር ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት የብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን እኩልነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ስሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።

ሀላፊው አክለውም ከመቸውም ግዜ በላይ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሸገር ፓርቲው ሴት አመራሮችን ወደ ለትላልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቶች በማብቃት በአህጉር ደረጃ ፈርቀዳጅ መሆኑን አክለው ፓርቲው አሸናፊው ሆኖ እንዲወጣ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የሀላባ ዞን የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ አሊማ ወርቁ በበኩላቸው በቀጣይ ወር ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫውን ስኬታማ ለማድረግ ሴቶች ቁልፍ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

ሀላፊዋ አያይዘውም በበላፉት ምርጫዎች ሴቶች በመራጭነት እንኳ ተሳትፏቸው የተቀዛቀዘ መሆኑን አንስተው ለዘንድሮው ምርጫ በነቂስ ወጥተው ስመዘገቡ መቆየታቸውን አክለው የተመዘገቡትን የምርጫ ካርዳቸው በጥንቃቄ በማስቀመጥ በምርጫው ቀንም በነቂስ ወጥተው እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ለሁሉም የመዋቅር የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ እንዲሁ ለዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ለሴቶች ክንፍ ህብረት የስንዴ ነዶ ምልክት ተበርክቶላቸዋል።

የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ እጩዎች ይፋ ሆኑ======ሚያዝያ 1/2018 ብልፅግና ...
09/04/2026

በ2018 ዓ.ም ለሚካሄደው በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ እጩዎች ይፋ ሆኑ
======

ሚያዝያ 1/2018 ብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ የሀላባ ዞንን በመወከል ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እና ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች ይፋ ሆነዋል።

በዚህ በመርሀ-ግብሩ ላይ በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር የሚወዳደሩ ዕጩዎች ቀርበው ለአባላቱ ተዋውቀዋል።

በዚህም መሰረት፦

➡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣
1.ዶክተር ነጃት ግርማ የፓርላማ አባል

➡ ለክልል ምክር ቤት

👉ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን (የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታ)

👉ዶክተር መሀመድ ኑርዬ በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሀላፊ፣

👉ክብርት መነቴ ሙንዲኖ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ፣

👉ወ/ሮ በይዳ ሙንዲኖ (የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ)

👉አቶ ሙህዲን ሁሴን (የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ)

👉 አቶ መሀመድከማል ኑርዬ (የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊና የዞኑ ዋና የመንግሥት ተጠሪ)

👉ገረድ ድልታታ ሙዜ (የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አባል)

በመድረኩ የፌዴራል፣ የክልልና ዞን ማዕከል፣ የወረዳ እና ከተማ የፓርቲና መንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇

ቴሌግራም፦ https://t.me/+eIbzwXJYyQNlYjVk

ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/profile.php?id=100083958027668

በቲክቶክበ፦ tiktok.com/

በቲውተር፦ https://x.com/Halabazonecomun?t=jrF0ELvPbOBJOuLT6X3G1A&s=09

ዋትስአፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029Vb3YNPxJZg4GKKQ3Om3v

ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/?si=SJOXf764DKjW1CUe

ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/halabazonecomunication?igsh=a3NwdTUwand6NWhn

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት ከተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍል ለተወጣጡ  ከባለድርሻ አካላት ጋር የማህጸን በር ካንሰር ክትባት ዙርያ ውይይት አደረገ(መጋቢት፣29/2018 ዓ.ም)ጉባ በሀላባ ዞን...
07/04/2026

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት ከተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍል ለተወጣጡ ከባለድርሻ አካላት ጋር የማህጸን በር ካንሰር ክትባት ዙርያ ውይይት አደረገ

(መጋቢት፣29/2018 ዓ.ም)ጉባ በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት ከተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍል ለተወጣጡ ከባለድርሻ አካላት ጋር የማህጸን በር ካንሰር ክትባት ዙርያ ውይይት አድርገዋል።

የዉይይት መድረኩን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙፍቲ አወል፣የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በርሶ ባሙድ ጋር በጋራ በመሆን መርተዋል።


የአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙፍቲ አወል የማህጸን በር ካንሰር በሴቶች ምንም ዓይነት ምልክት ሰያሳይ ከ19-20 ዓመት መቆየት ስለሚችል ምርመራ በማድረግ ቅድመ መከላከያ ክትባት በመከተብ መዳን እንደሚቻል ገልፀው የውይይቱ ተሳታፊዎች ለማኅበረሰቡ የማህጸን በር ካንሰር አስከፊነት በመግለጽ ምርመራ እንዲያደርጉና የክትባት መድኀኒት እንዲወስዱ የማስተባበር ኃላፊነት እንዲወጡ ተነግሯል ።


አያይዘውም የማህጸን በር ካንሰር መንስዔ፣ መተላለፊያ መንገዶችን፣ የማህጸን በር ካንሰር ዓይነቶችን እና በሴቶች ላይ ብቻ እንደሚከሰት በመግለጽ ምርመራ በማድረግና ክትባት በመስጠት መከላከል እንደሚቻል አብራርተዋል ።

የሚሰጠው ክትባት መድኀኒት መከላከያ የማህጸን በር ካንሰርን 100% በሽታውን መከላከል እንደሚችል እና ክትባቱ በዋናነት የሚሰጠው ከ9-14ዓመት ዕድሜ ክልል ለሚገኙ ልጃገረዶች ብቻ የሚሰጥ በመሆኑ የእናቶችም ሞት የሚያስቀር ክትባቱ አንድ ጊዜ ብቻ ከተወሰደ ለዕድሜ ልክ የሚከላከል መሆኑንም አቶ ሙፍቲ አወል አስረድተዋል ።

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በርሶ ባሙድ፦ክትባቱ ወረዳ ዉስጥ በሁሉም ቀበሌ በትምህርት ቤቶችና በሃይማኖት ተቋማት በቀበሌ ጣቢያ አከባቢዎች ስለሚሰጥ ማኅበረሰቡ የተሳሰተ ግንዛቤ እንዳይዝ ከአሉባልታ እንቆጠብ እና በ9 ዓመትና ከዚያ በላይ ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ልጃገረዶች ክትባቱን እንድወስዱ ማድረግ ከሁሉም የሚጠበቅ ኃላፊነት እንደሆነ ተነግሯል ።

አያይዘውም በወረዳው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የማህጸን በር ካንሰር ክትባት እንደሚሰጥ ገለጸው ሁሉም ትምህርት ቤቶች ለክትባቱ መሳካት የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

በመድረኩም የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በርሶ በሙድ የወረዳ ጤና ባለሙያዎች ፣ የቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ፣ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን ፣ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች ሌሎችም ባለድርሻ አካለቶች ተገኝተዋል ።

በሀላባ ዞን የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት

የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ቤተሰብ በተቋሙ ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አደረገ ።‎(መጋቢት፣29/2018) ‎የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ የ...
07/04/2026

የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ቤተሰብ በተቋሙ ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አደረገ ።
‎(መጋቢት፣29/2018)
‎የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ የብልጽግና ፓርቲ ቤተሰብ በዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያና በሌሎች ፓርቲ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አድርጓል።

‎ወይይቱን የመሩት የመምሪያው ምክትል የልማት እቅድ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪ አቶ በርገና ሚጦሬ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ከፊታችን ለሚመጣው ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የምርጫ ካርዱን በግዜ መወሰድ ያስፈልጋል ብለዋል ።

‎ከመልካም አስተዳደር አኳያ ማለትም በተቋሙ የስራ ሰዓትን ጠብቆ ከመግባትና መውጣት አንጻር ጥሩ ነገሮች መኖራቸውን የገለጹት አቶ በርገና ሚጦሬ ገልጸዋል ።
‎በውይይት መድረኩ ከፊታችን ባለው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ላይ በተቀመጡ ግቦች መሠረት እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ጥንካሬና የታዩ ጉድለቶች ዙሪያ እንዲሁም እስከ ምርጫ እለት ድረስ በተቀመጠው የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል ።
‎ከዚህም ባሻገር ተቋማዊ ስራዎች ላይ ማለትም የአምስት ሚሊየን ኢትዮኮደርስ ወቅታዊ አፈጻጸም እና ሌሎችም ወቅታዊ ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ።

ከዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን የተሰማራው የሱፐርቪዥን ቡድን የዞኑ የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት የተግባር አፈጻጸም  ምልከታ አደረገ።መጋቢ...
07/04/2026

ከዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን የተሰማራው የሱፐርቪዥን ቡድን የዞኑ የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት የተግባር አፈጻጸም ምልከታ አደረገ።

መጋቢት 28/2018 ዓ..ም

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የተሰማራው የሱፐርቪዥን ቡድን የዞን ማዕከል የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት የ3ተኛ ሩብ ዓመት የተግባር አፈጻጸምና የቅድመ ምርጫ ተግባራትን አስመልክቶ ምልከታ ማድረግ ጀምረዋል።

በዚህም መሠረት የሱፐርቪዥን ቡድኑ በዛሬው ዕለት
የዞኑን የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት በፓርቲ እና በኮሚሽን የ3ተኛ ሩብ ዓመት የተግባር አፈጻጸምና የቅድመ ምርጫ ተግባራትን አስመልክቶ ምልከታ አድርጓል።

ይህም በ3ኛ ሩብ አመቱ የተሰሩ የውስጠ ፓርቲ ስራዎችን እና የቅድመ ምርጫ ተግባራትን አፈጻጸም ላይ የተስተዋሉ
ጥንካሬዎች ለማስቀጠልና ድክመቶች ፈጥኖ ለማረም ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ግንባታን ለማጠናከር ሚና የጎላ ሚና አለው ተብሏል።

Address

Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share