የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Alaba K'ulito
  • የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት ይህ በሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት የፌስቡክ ገጽ ነው ።

16/09/2026
የሀላባ ዞን ኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባውን የመኖሪያ ቤት ቁልፍ አስረከበ====ጳጉሜ 2/2018 ​በሀላባ ዞን የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግ...
07/09/2026

የሀላባ ዞን ኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባውን የመኖሪያ ቤት ቁልፍ አስረከበ
====

ጳጉሜ 2/2018 ​በሀላባ ዞን የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት በአመራሩ፣በአባላቱ ንቁ ተሳትፎ እና ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባውን የብሎኬት መኖሪያ ቤት ለአቅመ ደካማው ለአቶ ኑሪዬ ሸ/መሀመድ የቁልፍ ርክክብ አድርገዋል።

የሀላባ ዞን የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት ጳጉሜ ሁለት ከማንሰራራት ቀን ምክንያት በማድረግ በህብረቷ አመራርና በአባሏ ንቁ ተሳትፎ እና ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር በዋንጀ ቀጠና ነዋሪ ለአቅመ ደከማ ለኑሪዬ ሸ/መሀመድ ያስገነባውን የብሎኬት ቤት የቁልፍ ርክክብ አድርጓል።

​ይህ በበጎ አድራጎት ስራ የተከናወነው የመኖሪያ ቤት ግንባታ የብልጽግና ፓርቲን ሰው ተኮር አቋም እና ለዜጎች የሚሰጠውን ቅድመ ሁኔታ የሌለው አክብሮትና ደጋፊነት በተግባር ያሳየ መሆኑ በቁልፍ ርክክብ ስነስርዓት ላይ ተገልጿል።

​በቁልፍ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የዞኑ እና የህብረቱ አመራሮች ባስተላለፉት መልእክት፣ብልጽግና ፓርቲ በፖሊሲው እና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ሰውን ማዕከል ያደረገ ልማትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

አክለውም፣«የፓርቲያችን ዋና ዓላማ የዜጎችን እንግልትና ችግር መቅረፍ ነው» በማለት፣ መሰል ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ማድረግ የሁሉም አካል ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል።

​የቤቱ ባለቤት አቅመ ደካማ ኑሪዬ ሸ/መሀመድ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል ይኖሩበት የነበረው ቤት ለችግርና ለእንግልት ይዳርጋቸው እንደነበር አስታውሰው፣ችግሩን ለመቅረፍ ብልጽግና ፓርቲ አሁን በተደረገላቸው ድጋፍ አዲስና ደረጃውን የጠበቀ የብሎኬት ቤት ባለቤት በመሆናቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልጸዋል።ለአመራሩ፣ለህብረቱ አባላት እና ለህብረተሰብም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​በዝግጅቱ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት አቶ ሱሊማን ሀሰን የሀላባ ዞን ኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት ሰብሳቢና የሀላባ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ እንደገለፁት የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን በማጎልበት የህብረቷ በአመራሩዋና በአባሏ ንቁ ተሳትፎ እና ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አዲስና ደረጃውን የጠበቀ የብሎኬት ቤት በማስገንባትና ሙሉ ቤት የውስጥ ቁሳቁስ በሟሟላት በዛሬ እለት ርክክብ ተደርጓል።

ከዚህም በተጨማሪ የአቅመ ደካማውን የኢኮኖሚ አቅም በቀጣይነት ለማጎልበትም ሱቅና የውስጥ ቁሳቁስ በሟሟላት ቋሚ የሥራ እድል የመፍጠር ተግባር መከናወኑንም አቶ ሱሊማን ተናግሯል።

አቶ ሃጂ ኑሪዬ የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሀላፊ በበኩላቸው የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን የሚያጎለብት በመሆኑ ሊመሰግኑ እንደሚገባ ገልጸው፣ በቀጣይም ለአቅመ ደካሞች የሚደረጉ መሰል ድጋፎች ተጠናከረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር መሆኑን ይህ ማሳያ መሆኑንም አቶ ሃጂ ተናግሯል።

​ይህ የቁልፍ ርክክብ ፕሮግራም የብልጽግና ፓርቲን ሰው ተኮር መመሪያ በስራ ላይ በማዋል፣ የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል የሚደረገውን ጥረት በተግባር ያሳየ አጋጣሚ መሆኑ ተገልጿል

በቁልፍ ርክክብ ፕሮግራሙ ላይ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣የኢኮኖሚ ቁጥር ሁለት ብልጽግና ህብረት አመራሮች እና አባላት፣የከተማው ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች፣ የከተማው ከንቲባ ሌሎችም

በሀላባ ቁሊቶ አጠቀላይ ሆስፒታል ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ተግባር  ተካሄደ!!‎‎  የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞንና የከንባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በትብብር በሀላባ ...
05/09/2026

በሀላባ ቁሊቶ አጠቀላይ ሆስፒታል ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ተግባር ተካሄደ!!

‎ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞንና የከንባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በትብብር በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ተግባር አከናወኑ።

‎በዚህ በጎ ተግባር መርሃ ግብር ወጣቶቹ በሀላባ ቁሊቶ አጠቃላይ ሆስፒታል በመገኘት ህሙማንን በመጠየቅ የማበረታቻና የወዳጅነት መልዕክት በማስተላለፍ ከህሙማን ጋር የሚያሳየውን ሰብዓዊ ትስስር አጠናክረዋል።

‎በተጨማሪም ለሆስፒታሉ ህሙማን ፈሳሽ ጁስ ድጋፍ በማድረግ በህክምና ላይ ለሚገኙ ወገኖች ተጨማሪ የሞራል ድጋፍ አድርገዋል።

‎ይህም በጎ ተግባር በአንድ ቦታ ብቻ የሚወሰን ሳይሆን ከአካባቢ ወሰን በላይ በመስፋት ለማህበረሰቡ የመተሳሰብ የመረዳዳትና የአብሮነት እሴቶችን ለማጠናከር የሚያግዝ ተግባር እንደሆነ ተገልጿል።

‎በበጎ ተግባሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብድ ድንቁና፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አ/መጅድ ፊጣሞ እንዲሁም ሌሎች የከተማና የዞን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

‎አመራሮቹና ወጣቶቹ በሆስፒታሉ በመገኘት ህሙማንን በመጠየቅ ያሳዩት ተሳትፎ በችግር ወቅት ከወገኖች ጎን መቆም የሚገባውን ሰብዓዊ ኃላፊነት የሚያሳይ ነው።

‎ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ተግባሩም የወጣቶችን የበጎ ፈቃድ ተሳትፎ በማጠናከር የመረዳዳትና የአብሮነት ባህልን በማስፋት እና በችግር ወቅት ወገኖችን መደገፍ እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ሆኗል።

የሀላባ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት የነሀሴ ወር ስራ አፈጻጸምና ቀጣይ ሥራ አቅጣጫ ዙሪያ በZoom meeting /በበይነመረብ/ዉይይት አደረገ ። ነሃሴ 29...
05/09/2026

የሀላባ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት የነሀሴ ወር ስራ አፈጻጸምና ቀጣይ ሥራ አቅጣጫ ዙሪያ በZoom meeting /በበይነመረብ/ዉይይት አደረገ ።

ነሃሴ 29/2018 ዓ.ም
ቁሊቶ

የሀላባ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊዎች ጋር በመሆን በነሀሴ ወር የተከናወኑ ስራዎችንና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በZoom meeting ገምግሟል።

የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን የመሩት የሀላባ ዞን የብልፅግና የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር መዲና ዓለሙ ሲሆኑ የግምገማውን አጀንዳዎችን አቅርበው በተለይም የኮሚሽኑን ተግባራት በአንድ ዕቅድ፣ አንድ ሪፖርት፣ አንድ ምዘና መርህ ለማከናወን በሚረዳ መልኩ መከናወን እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። በዚሁ መሠረት የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊዎች የነሀሴ ወር አፈጻጸም ሪፓርት አቅርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥም የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል።

ጠንካራ ኢንስፔክሽን፤ ለጠንካራ ፓርቲ!

እንኳን ደሥ ኣላችሁ/አለን!! የማእከላዊ ክልል ጤና ቢሮ በ2018 አመታዊ ጉባኤ ማጠቃላያ በአጠቃላይ የጤና ዘርፍ የተሻላ አፈጻጸም በመመዝገቡ ለዞናችን  ጤና መምሪያ(ከክልሉ 2ኛ)፣ለሀላባ ቁ...
01/09/2026

እንኳን ደሥ ኣላችሁ/አለን!!

የማእከላዊ ክልል ጤና ቢሮ በ2018 አመታዊ ጉባኤ ማጠቃላያ በአጠቃላይ የጤና ዘርፍ የተሻላ አፈጻጸም በመመዝገቡ ለዞናችን ጤና መምሪያ(ከክልሉ 2ኛ)፣ለሀላባ ቁሊቶ ከተማ አሥተዳደርና ለዌራ ወረዳ አስተዳደር ዕዉቅናና ሽልማት ተበርክቷል...!!!

የማህበረሠባችንን ጤና ለመጠበቅና አጠቃላይ የጤና አገልግሎቱን ለማሻሻል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጃት በ2018 በርካታ ተግባራትን ለማሳካት ተሟክሯል።ይህ በጤናው ዘርፍ የታየው ውጤት የብዙ ባለሙያዎች የሌሊትና የቀን ድካም፣ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ቅንጅት፣ የቁርጠኝነት እና የተጋድሎ ፍሬ ነው::በመሆኑም ይህ የእውቅና ሽልማት በሰራነው ረክተን የምንዘናጋበት ሳይሆን ለቀጣይ ትልቅ የቤት ስራ የሚያዘጋጀን የህዝባችን አደረ መልዕክት፤ ለጤናው ማህበረሰብ የሞራልና ብርታት ስንቅ መሆኑን ተረድተን በተሻለ ትጋትና በላቀ አፈፃፀም የጤናውን ዘርፍ ስኬት የሚናፀናበትና ደረጃ በደረጃ የጤናዉን አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራት ለማሻሻልና በዞናችን የማይበገር የጤና ስርኣት እዉን ለማድረግ ሁላችንም የተለመደዉን ርብርብ ማድረግ ይጠበቅብናል።..ጤና ኤክስቴንሺኖቻችን፣የጤና ባለሙያወችና ሠራተኞች፣የጤናዉ አመራሮች፣የዞን ወረዳ/ከተማ የመንግስትና ፓርቲ አመራሮችን፣የዞኑን ማህበረሰብ፣የሚድያ አካላት፣ ክልል ጤና ቤሮ እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን ከልብ እናመሠግናለን...🙏

በድጋሚ እንኳን ደሥ ኣላችሁ/ኣለን!!

‎የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ከወረዳ ፣ከከተማና ከዞን ህብረቶች  የብልጽግና ፓርቲ የእንስፔክሽንና ስነ-ምግባርኮሚሽን ጋር የ2018 ዓ/ም እቅድ አፈጻጸም የማጠ...
01/09/2026

‎የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ከወረዳ ፣ከከተማና ከዞን ህብረቶች የብልጽግና ፓርቲ የእንስፔክሽንና ስነ-ምግባርኮሚሽን ጋር የ2018 ዓ/ም እቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ ግምገማ እና 2019 በጀት አመት እቅድ መግባቢያ መድረክ ተካሄደዋል ።

‎መድረኩን የመሩት የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ሀላፊ እንጂነር መዲና አለሙ የአመራሩንና የአባላቱን ሥነ-ምግባር ማሳደግ፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን መታገል እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥን ግልጽና ተጠያቂነት ያለው በማድረግ ጠንካራ ስራዎች መሰረታቸውን ገልፀው ይህም ቀጣይ ከምንግዜውም በላይ የተሻለ ዉጤታማ ለመሆን የኮሚሽኑ አባለት ሚና ወሳኝ ነው ብሏል።

‎በየደረጃው በሚገኙ የፓርቲ መዋቅሮች ውስጥ የፋይናንስና የንብረት አጠቃቀም ህግና ደንብን የተከተለ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም ኢንጂነር አክለዋል ።

‎በዞን፣ ወረዳና ከተማ ደረጃ የሚገኙ የኮሚሽኑ የመዋቅር አካላት የቁጥጥር አቅማቸውን በማሳደግ ቅድመ-መከላከል ላይ ያተኮረ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባቸው በአጽንኦት ተነግሯል ።

‎የሀላባ ዞን የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽን ስነምግባር ኮሚሽን ሰብሳብ አቶ መሀመድ ሀሰን በየደረጃው ለሚገኙ የኮሚሽኑ አካላት ወቅታዊ የአሰራርና የቁጥጥር ስልጠናዎችን በመስጠት አፈጻጸምን ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረው የፓርቲውን ህግና ደንብ የሚጥሱ አሰራሮችን በጥብቅ በመከታተል በመመሪያዉ መሠረት የእርምት እርምጃዎችን በወቅቱ መውሰድ ይገባል ብሏል
‎​
‎አቶ መሀመድ አክለዉም ከአባላትና ከህዝብ የሚነሱ ቅሬታዎችን በፍጥነትና በፍትሃዊነት የሚያስተናግድ አሰራርን የበለጠ ማጠናከር ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ መሰረት መሆኑን በትኩረት ገልጿል ።

‎የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ፦ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የቁጥጥር፣ የክትትልና የኢንስፔክሽን ሥራዎች በዝርዝር በቀረበው ሰነድ ዙሪያ እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ሰፈ ያለ ዉይይት ተደርጓል ።

‎በመጨረሻም ኮሚሽኑ ከሁሉም መዋቅር ጽ/ቤቶች እና ከህብረቶች ጋር የጋራ የግብ ስምምነት የተፈራረሙ ስሆን በበጀት አመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡት የኮምፒወተር;የዋንጫ: የሰርተፍኬትና: የጽሀፈት መሠሪያዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ::

‎በመድረኩም ላይ የሀላባ ዞን ህግና እና አስተደደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ሁሴን እብራህም የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢዎች: የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና የዞኑ የሁሉም የህብረቶች አመራርና አባላቶች ተገኝተዋል ።


‎ጠንካራ እንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ

 #ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ!!፣‎የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን በዞኑ ስር ከሚገኙ የታችኛው መዋቅሮች ጋር በ2018 ዓ/ም እቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ...
01/09/2026

#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ!!፣
‎የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን በዞኑ ስር ከሚገኙ የታችኛው መዋቅሮች ጋር በ2018 ዓ/ም እቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ ግምገማ እና 2019 ዓ/ም እቅድ መግባቢያ መድረክ አካሄደ

የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን በዞኑ ስር ከሚገኙ ከወረዳ ፣ከከተማና ከ ከዞን ህብረቶች የብልጽግና ፓርቲ የእንስፔክሽንና ስነ-ምግባርኮሚሽን ጋር የ2018 ዓ/ም እቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ ግምገማ እና 2019 በጀት አመት እቅድ መግባቢያ መድረክ አካሄደዋል።

‎በመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ም/ሀላፊ እና የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፍ አቶ አደም ጀማል 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በተጠናቀቀበትና ፓርቲያችን በክልልና በፌዴራል ምክር ቤቶች አብላጫ ድምጽ ማግኘቱ በምርጫ ቦርድ በተገለጸበት ማግስት መካሄዱ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሀገራችንን የአንድነታችንን መሳያ የብልጽግና ጉዞአችንን በድል የሚያስመሰግን ሆኖ መጠናቀቁ መድረኩን የተለየ ያደርገዋል ብሏል።

‎በዚህም የኢንስፔክሽን ስነምግባር ኮሚሽን የፓርቲውን ውስጣዊ አሰራር እና ህግ ለማስከበር የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው የኮሚሽኑ ዋነኛ ዓላማ ጥፋተኞችን መቅጣት ብቻ ሳይሆን የሙስና እና የስነ-ምግባር ጉድለቶች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ የመከላከልና የማረም ባህልን ማዳበር እንደሆነ በመናገር መድረኩን በይፈ አስጀምረዋል

‎የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ሀላፊ እንጂነር መዲና አለሙ በበኩላቸው ኮሚሽኑን እስከታችኛው መዋቅር የማጠናከር፣ተቋማዊ አቅሙን የማጎልበት፣በሰው ሀይል የማደራጀት፣ምቹ የስራ አካባቢን መፍጠርና የውስጥ አሰራር ስርዓትን የመዘርጋት የተቀናጁ ስራዎች መሰራታቸውንም አብራርተው በሁሉም መዋቅሮች የሚገኙ የኮሚሽኑ አካላት የፓርቲውን መሪዎችና አሰራሮችን አሰራሮች በጥብቅ በመከተል የህዝብን እምነት የሚያጎለብት የቁጥጥር ስራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

‎ለመድረኩ የተዘጋጀውን ሰነድ የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ሀላፊ እንጂነር መዲና አለሙ እና በም/ሀላፊ በሆኑት አቶ ሰፍሮ መሀመድ አቅርቧል ።

‎በመጨረሻም የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ እና የእዉቅና መርሃግብር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል ።

‎በመድረኩም ላይ የሀላባ ዞን ህግና እና አስተደደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳብ የተከበሩ ሁሴን እብራህም የሀላባ ዞን የብልፅግና የእንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽ የኮሚሽኑ አባለት የሁሉም መዋቀር የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና ሰብሳብዎች የዞኑ የሁሉም የህብረት አባላት ተወካዮች ተገኝተዋል ።

‎ሲል የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽህፈት ቤት ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ዘግቧል


ለጠንካራ ፓርቲ ተቋም ግንባታ፡ የ2019 በጀት ዓመት የእቅድና የፈጻሚ ዝግጅት ግምገማ ተካሄደ!ሆሳዕና ፣ ነሐሴ 22/2018 ​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና የሥነ...
29/08/2026

ለጠንካራ ፓርቲ ተቋም ግንባታ፡ የ2019 በጀት ዓመት የእቅድና የፈጻሚ ዝግጅት ግምገማ ተካሄደ!
ሆሳዕና ፣ ነሐሴ 22/2018
​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ እና የፈጻሚ ዝግጅት ተግባራትን አፈጻጸም ከዞንና ከልዩ ወረዳ የኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤቶች ጋር በበየነ-መረብ (Online) ገምግሟል።
​በመድረኩ የኮሚሽኑ ቅ/ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል፣ ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሂሩት ተሾመ፣ እንዲሁም የዞንና የልዩ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ዋናና ምክትል ሃላፊዎች ተገኝተው የተሳተፉ ሲሆን፣ በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ የጋራ መግባባት ተደርሷል።

• ​የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም፡ በ2019 በጀት ዓመት «አንድ እቅድ፣ አንድ ሪፖርት፣ አንድ ምዘና» መርህን መሰረት በማድረግ የተቀደው እቅድ ላይ ለአመራሮች፣ አባላትና ባለድርሻ አካላት ኦሪንቴሽን በመስጠት ጠንካራ የፈጻሚ ዝግጅት መደረጉ እና አንድ ደረጃ ዝቅ ካሉ አደረጃጀቶች ጋር የግብ ስምምነት መፈራረም መቻሉ ተገምግሟል።
• ​የተቋም አቅም ግንባታ፡ የ2018 ስኬቶችን በማስፋትና ክፍተቶችን በማረም የ2019ን እቅድ አፈጻጸም የበለጠ ማላቅ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን፣ በየደረጃው ያሉ ቅ/ጽ/ቤቶችን በግብዓትና በጠንካራ የአመራር ስምሪት ማጠናከር እንደሚገባ ተመላክቷል።

• ​የአሰራር ሥርዓትና ክትትል፡ የኮሚሽኑን አሰራሮች በዲሲፕሊን በመፈጸም ተቋማዊ ባህልን መገንባት፣ እንዲሁም ተልዕኮን በጥራት ለመወጣት ተከታታይነት ያለው የድጋፍ፣ የክትትልና የግብረ-መልስ ስርዓት በማበጀት መስራት እንደሚያስፈልግ ተስመሮበታል።
• ​የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ትኩረት፡ በብቁ ዝግጅት ላይ የተመሰረተ የ2019 አንደኛ ሩብ ዓመት ኢንስፔክሽን በአራቱ የትኩረት መስኮች ላይ በማካሄድ፣ ግኝቶችን ከምክረ-ሃሳብ ጋር በማቅረብ ለፓርቲው የሚቆጠር እሴት ለመጨመር ቁርጠኝነት ተይዟል።
​ኮሚሽናችን አሰራሩን በማጠናከር ለጠንካራ ፓርቲ ተቋም ግንባታ የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አጠናክሮ ይቀጥላል!

በተቋማት የሚስተዋሉ የብልሹ አስራርና አመራር ላይ የሚደርገው  የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላከተ! #ሆሳዕና ነሀሴ 18/2018 የምስራቅ ጉ...
24/08/2026

በተቋማት የሚስተዋሉ የብልሹ አስራርና አመራር ላይ የሚደርገው የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላከተ!

#ሆሳዕና ነሀሴ 18/2018

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀተ ዓመት ሪፖርት ግምገማና የ2019 ዕቅድ ላይ የምክክር መድረክ አካሄዷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዳነ ተሰማ እንደገለፁት በብልሹ አስራርና አመራር ላይ የምናደርገው የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ የመውሰድ ተልዕኮ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

የዞኑ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የፈፀማቸው ተግባራት በጥሩ ደረጃ እንዳለ ከግምገማ ሪፖርቱ ማረጋገጥ እንደቻሉ የተናገሩት አቶ አዳነ በቀጣይ የኮሚሽኑ ተግባራት እስከ ወረዳ፣ ከተማና ቀበሌ ድረስ የአደረጃጀትና የአሰራር ስርዓታችን እንዲጎለብት መትጋት አለብን ብለዋል።

በየመዋቅሩ ያሉ የህብረት ኮሚሽኖች ቢያንስ በየሩብ ዓመት የክትትልና ድጋፍ በማድረግ ክፍተቶች በማመላከት እንዲታረሙ ማድረግ፣ የኮሚሽን አመራሩና አባላቱ ኃላፊነታቸው በመወጣት የድርሻቸው ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሙንታሃ ሽሁር በማጠቃለያ መድረኩ ላይ እንደተናገሩት በተቋማት ደረጃ የሚስተዋሉ የአሰራር ግድፈቶች ማስቆም የሚችል ተቋማዊ አሰራርና አመራር መግንባት እንደሚገባ አመላክተዋል።

በዞኑ ኮሚሽንና በመዋቅሮች የኮሚሽን ተቋማት መካከል ያለው የግንኙነት ሥርዓት ይበልጥ በማሳደግ ድክመቶች በየጊዜው እየገመገሙ የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዲስተካከሉ በማስቻል የኢንስፔክሽን ሥራውው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል።

ኃላፊዋ አክለውም በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት ሁሉም የኮሚሽን ተቋማት ያለቸው የመፈፀም አቅም በማሳደግ እንዲተጉ አሳስበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ በበኩላቸው በአሰራር ብልሹነት ምክንያት የሚፈጠሩ ህዝባዊ ቅሬታዎች ምላሽ መስጠት የሚችል ጠንካራ የኢንስፕክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ተቋም መገንባት እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

የክትትልና ድጋፍ ሥራችን በትክክል ክፍተቶች ለይቶ መፍትሔ እንዲያገኙ ማመላከት የሚችሉ መሆን አለባቸው ብለዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊ አካላትም የኮሚሽኑ አሰራሮች ደንቦችና የዲስፕሊን አመራር ሥርዓት ለህዝብ ለማድረስ ተቋሙ የሚዲያ ፕላትፎርሞች በሚገባ ጥቅም ላይ በማዋል በነቃ ተሳትፎ የመረጃ ተደራሽነቱ ማሳደግ እንደሚገባ ምክረ-ሀሳብ ተስጥቷል።

በየመዋቅሩ ያሉ አደረጃጀቶችና የመረጃ ሥርዓት ጥንካሬዎቹ በማስቀጠል ያሉባቸው ጉድለቶች ፈጥነው በማስተካከል ለኮሚሽኑ ጥቅል ውጤታማነት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ከመደረክ ተሳታፊ አካል ተመላክቷል።

በመድረኩ መጨረሻ የዞኑ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ከየመዋቅሩ ኮሚሽን ቅ/ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የግብ ስምምነት በመፈራረምና ለባለ ድርሻ ተቋማትና የምስክር ወረቀትና በ2018 በጀት ዓመት የላቀ የአፈፃፀም ውጤት ላስመዘገቡ የኮሚሸን ጽ/ቤቶች ዕውቅና የዋንጫ፣ የገንዘብና ምስክር ወረቀት ሽልማት ሰጥቷል። በዚሁ መሠረት፦

1ኛ የሶዶ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት፦ የዋንጫ የ40 ሺ ብር እና የምስክር ወረቀት

Address

Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሺንና ስነ ምግባር ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share