05/06/2026
በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በ(UNFPA) ፕሮግራም ከተለያዩ ቀበሌዎች ለተወጣጡ ለስራ አጥ ወጣቶች በስራ ፈጠራ አስተሳሰብና ክህሎት ዙሪያ የተዘጋጀ ስልጠና ተሰጠ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ እንድሁም በዞኑና በወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስተባባሪነት በ(UNFPA) ፕሮግራም ከተለያዩ ቀበሌዎች ለተወጣጡ ለስራ አጥ ወጣቶች በስራ ፈጠራ አስተሳሰብና ክህሎት ዙሪያ የተዘጋጀ ስልጠና ተሰጥቷል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙንድኖ በፈታ በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት ስሆን፣በዚህም ወቅት ሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዱን በትኩረት በመከታተል፣በቀጣይ በስራ ፈጠራና በአስተሳሰብ ክህሎት ላይ ያላቸውን ሚና ለማሳደግ እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።
የግንዛቤ ማስጨበጫው በሀላባ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የስብዕና ልማት ስራዎች ዳይሬሰቶሬት አቶ ታሪኩ ሶደኖ አማካኝነት በሰፊው ተብራርቶ ቀርቧል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙንድኖ በፈታ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትልና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብደላህ አደምን ጨምሮ የጽህፈት ቤቱ የማኔጅመንት አካላት፣ከተለያዩ ቀበሌዎች የተወጣጡ ስራ አጥ ወጣቶችና ሴቶች ተገኝተዋል።
✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ግንቦት 28/2018 በሸኖ፣