30/01/2022
በአፉር ክልል የስፖርት ለሁሉም የንቅናቄ መርሃግብር ማስጀመሪያ መድረክ በአይሳኢታና በአዋሽ-7 ኪሎ ከተሞች ተካሄደ፡፡
**************************************************
“ስፖርት ለሁሉም!!! ሁሉም ለስፖርት” ሚል መሪ ቃል ከጥ 22/2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 30/2014 ዓ.ም ድረስ የሚቀይ የአፋር ክልል የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴና የስፖርት ለሁሉም የንቅናቄ መርሃግብር ማስጀመሪያ መድረክ በአይሳኢታ እና በአዋሽ-7 ከተሞች የተካሄደ ሲሆን በአይሳኢታ ከተማ የወረዳና የከተማ መስተዳድር አመራሮችና ነዋሪዎች እንዲሁም ታዋቂ አርቲስቶች የተሳተፉ የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የ3 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የእግር ጉዞ የተካሄደ ሲሆን በአጠቃላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው 210 ተማሪዎች፣ 125 የመንግስት ሰራተኞች እና 245 የከተማው ማህበረሰብ ተሳትፈውበታ፡፡
በተመሳሳይ በአዋሽ-7 ኪሎ ከተማ በተካሄደው የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ 109 ተማሪዎች፣ 77 የመንግስት ሰራተኞች እና 99 የከተማው ማህበረሰብ የተሳተፉ ሲሆን በተጨማሪ በንቅናቄ መርሃ ግብሩ በጦርነቱ ለተጎዱ የደም ልገሳ ስነስርዓት ተካሂዷል፡፡
በቀጣይም እስከ ግንቦት 30/2014 ዓ. ም ድረስ በክልሉ በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ መሰተዳድሮች በተከታታይ በሚዘጋጁ የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴና የስፖርት ለሁሉም የንቅናቄ መርሃግብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአፋር ክልል የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አመራሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች እያበረታቱና እየደገፉ ይገኛሉ፡፡