02/04/2026
ዜና ችሎተ
ከባድ ስርቆት እና መሸሸግ ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች በ3 ዓመት ከ 9 ወር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል
ከሳሸ አቃቢ ህግ
ተከሳሽ 1 ቻሌ ሞላ አሰሜ
2. ሲሳይ አለምነው እምሬ አድራሻቸዉ በለሳ ወረዳ ዋርካ ቀበሌ የሆኑት ግለሰቦች በ1996 ዓ/ም ተደንግጎ የወጣዉን የኢፌደድሪ የወንጀል ህግ ድንጋጌ አንቀፀ 32/1/ /ሀ/እና 669 /3/ /ለ/ ን በመተላለፍ ተገቢ ያልሆነ ሃብት ለማግኘት በማሰብ አንድ ካልተታዘ ግለሰብ ጋር በመሆን በቀን 18 /06 /2018 ዓ ም ከሌሊቱ 7 00 ስዓት ሲሆን በአዲስ ዘመን ከተማ ቀበሌ 03 ልዪ ቦታዉ ፍተሻ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራዉ ቦታ የግል ተበዳይ የአቶ ጌታቸዉ በእዉቀትን የኮንቲነር ሱቅ ሰብረዉ በመግባት የተለያዪ የሱቅ እቃዎችን የወሰዱ በመሆኑ በፈፀሙት ስርቆት ወንጀል ተከሰዋል ተከሳሾችም በተባለዉ ቀንና ስዓት ድርጊቱን አልፈፀምነም ብለዉ ክደዉ ተከራክረዋል ፍ/ቤቱም አቃቢ ህግ ምስክሮችን እንዲያቀርብ ብይን ተሰጥቶ የአቃቢ ህግ ምስክሮችም እንደክሱ አስረድተዋል፡፡ ተከሳሾችም የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ ቢጠየቁም ክሱን ማስተባበል አልቻሉም ፡፡ ፍርድ ቤቱም በ10 /7/2018ዓ.ም ይዞት በዋለው ችሎት ጥፋተኞችን ያርማል ያስተምራል መሰል የማሀበረሰብ ክፍሎችንም ያስጠነቅቃል በሚል በ3 ዓመት ከ 9 ወር እንዲቀጡ ፍረድ ቤቱ ወስኗል