04/06/2026
የአራተኛ ሩብ ዓመት የወረዳዎች ድጋፍና ክትትል ግብረመልስ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።
===============================
25/9/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ
የአቃቂ ቃሊቲ የስራና ክህሎት ጽ/ቤት በስሩ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች የአራተኛ ሩብ ዓመት ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በተገኙ ውጤቶችና መስተካከል ባለባቸው ግብረመልሶች ዙሪያ ከወረዳዎች የዘርፉ ብድን መሪዎችና አስተባባሪዎች ጋር የጋራ መድረክ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተለዩ ክፍተቶችና በጥንካሬ የሚወሰዱ ግኝቶች ተጠምረው የቀረቡ ሲሆን በመድረኩ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት የጽ/ቤቱ ም/ኃላፊ አቶ ዘነበ ወዬሳ ይህ ኦዲት መሰል ድጋፍና ክትትል ሁሉም ወረዳ ያለበትን ቁመና በግልፅ ያመላከተ መሆኑን ገልፀው የዓመቱ መጨረሻ ላይ የምንገኝ እንደመሆናችን በክፍተት የታዩ ስራዎች በከፍተኛ ተኩረት በቀናት ውስጥ ተጠናቀው መቀረብ ያለባቸው መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በመጨረሻም የዚህ ዓመት አፈጻጸማችን እንደ ከዚህ ቀደሙ ቀዳሚ በመሆን በውጤት እንደሚደመደመ መግባባት ላይ ተደርሷል።