31/07/2025
የድርሻችንን ተወጥተናል!!
ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት የ 2017 የአረንጏዴ አሻራ መርሀ-ግብር አከናውኗል::
በዛሬው እለት ከማለዳው አስራ ሁለት ሰዓት ጀምሮ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ውጥን መሰረት "በመትከል ማንሰራራት” የሚለውን መሪ ቃል በማንገብ የፅ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ሳምራዊት አማን በተገኙበት እንዲሁም ሁሉም የአካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት ባለሙያዎች በወረዳ 4 አቃቂ ወንዝ ዳርቻ በመገኘት አሻራቸውን አኑረዋል::
ወቅታዊ እና በአካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት የሚሰጡ አገልግሎቶችንና መረጃዎችን ለማግኘት ሲፈልጉ ይህን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ይከተሉ !