የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ Morning Star for Ethiopia

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ Morning Star for Ethiopia የንጋት ኮኮብ ለኢትዮጵያ በምርጫ ቦርድ ቅድመ እውቅና የተሰጠው አገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመስራት የመስራች ጉባዔውን ለማድረግ በመደራጀት ላይ የሚገኝ ነው።

አንጋፋው የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ፕ/ር በፍቃዱ ደግፌ አረፉ:: በምርጫ 2013 ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለሀገራችን የፖለቲካ ስብራት መቃናት  የራሳቸውን አስተዋፅኦ ያደረጉና ለብዙ ምሁራንም ወደ ፖ...
09/01/2025

አንጋፋው የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ፕ/ር በፍቃዱ ደግፌ አረፉ::
በምርጫ 2013 ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ለሀገራችን የፖለቲካ ስብራት መቃናት የራሳቸውን አስተዋፅኦ ያደረጉና ለብዙ ምሁራንም ወደ ፖለቲካው መድረክ እንዲመጡ አርአያ የሆኑ አንጋፋ ሰውም ነበሩ።
በፕሮፌሰሩ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው፣ ዘመዶቻቸው እና ጓዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!     የምስረታ ሂደቱን በማጠናቀቅ ላይ የሚገኘው እና በቅርቡም ለሚደረገው   ዝግጅት...
07/01/2025

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
የምስረታ ሂደቱን በማጠናቀቅ ላይ የሚገኘው እና በቅርቡም ለሚደረገው ዝግጅት ላይ የሚገኘው
ለአባላትና ደጋፊዎቻችን እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ በዓሉ የሰላም ፣የደስታ እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እየተመኘን በዓሉን ስናከብር በተለመደው ኢትዮጵያዊ እሴቶቻችን በጋራ እና በአብሮነት የተቸገሩትንም በመርዳት መሆን እንዳለበት ለማስታወስ እንወዳለን!!

መልካም በዓል!!

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲን መቀላቀል እና አባል መሆን የምትፈልጉ ከዚህ ቀጥሎ ያለውን Link በመጠቀም ፎርም መሙላት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።👇👇
06/11/2024

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲን መቀላቀል እና አባል መሆን የምትፈልጉ ከዚህ ቀጥሎ ያለውን Link በመጠቀም ፎርም መሙላት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።👇👇

"የንጋት ኮኮብ ለኢትዮጵያ" በሚል ስያሜ አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት ከምርጫ ቦርድ የጊዜያዊ ፍቃድ በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ዜግነትን መሠረት ያደረገ ፓርቲ ለመመስረት በሂደት ...

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ቅድመ ምሥረታ ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳያካሂድ መከልከሉን በማስመልከት የተሰጠ መግለጫ። የኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል በአገዛዙ መጠን ሰፊ አፈና  ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደቁልቁለት...
23/10/2024

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ቅድመ ምሥረታ ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳያካሂድ መከልከሉን በማስመልከት የተሰጠ መግለጫ።

የኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል በአገዛዙ መጠን ሰፊ አፈና ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደቁልቁለት እየተንደረደረ ቢገኝም ለሀገር አንድነት፣ ሕዝባችን የተነፈገውን መሠረታዊ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ መብቶች ለማስከበር፣ ለብዙ ዘመናት ብዙ ዋጋ የተከፈለለትን ዴሞክራሲን ለማግኘት ከሕዝብ ጋር በተባበረ ክንድ የጋራ ትግል ለማድረግ "የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ" በሚል ስያሜ ከምርጫ ቦርድ ያገኘውን ቅድም እውቅና በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት እና ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎቻችን በይፋ ለማሳወቅ ለመንግሥትና ለግል ሚዲያዎች ይፋዊ ጥሪ በማድረግ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል መግለጫ ለመስጠት በተዘጋጀንበት ወቅት ያለበቂ ምክንያት በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳይሰጥ ክልክላ ተደርጓል።

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ከሥርዓቱ ቀደምት ባህሪ በመነሳት እንዲህ ዓይነት ተግዳሮቶች እንደሚገጥመው ቢያውቅም አሁን ያለው መገፋት ከሕዝብ ጎን እንዲቆም ትግሉን በተጠናከረ መልኩ እንዲያካሂድ የሚያነሳሳው በመሆኑ ከምርጫ ቦርድ እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የተከለከለውን መግለጫ ለመስጠት ጥረት ያደርጋል።

በዚሁ አጋጣሚ ጋዜጣዊ መግለጫው እንዳይደረግ ላደረጋችሁ አካላት ትግላችን ለሁላችንም የምትመች አገር እንድትኖረን በማሰብ መሆኑን በመረዳት ከመሰል ድርጊታችሁ እንድትታቀቡ አበክረን እንጠይቃለን።

አደራጅ ኮሚቴው በቀጣይ በተለያዩ ከተሞች ተንቀሳቅሶ ስለ ኢትዮጵያ ንጋት የሚሰራውን ፓርቲ የማደራጀት ስራ እንደሚቀጥል በመዋቅሩ ውስጥ ላሉ ሰላማዊ ታጋዮች ያሳውቃል።

ይነጋል!

ጥቅምት 13; 2017 ዓ.ም

አዲስአበባ

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ የአደራጅ ኮሚቴ ሕዝብ ግንኙነት

ለለጠ መረጃ
Telegram👇

https://t.me/Morningstar4Eth

Facebook👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=61564830160380

Tiktok👇
tiktok.com/

22/10/2024

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913521350

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ Morning Star for Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share