19/11/2022
ማዕከሉ ከአፋር የማዕድን ልማት አክሲዮን ማህበር ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
***************************************************************
የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ከአፋር የማዕድን ልማት አክሲዮን ማህበር ጋር በክሎርአልካሊ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
በክሎርአልካሊ የኬሚካል ኢንዱስትሪ ላይ ቴክኒካል እና ቅድመ የአዋጭነት ጥናት ማካሄድ ለስራው አስፈላጊ የሰው ሀይል መመደብ፣ ወቅታዊ ሪፖርት አዘጋጅቶ መላክ፣ ከተቋማት የተሻለ ተሞክሮ መቀመርና የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ስራ መስራት ለማዕከሉ ተሰጡ የስራ ሀላፊነቶች ሲሆኑ አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ፣ ለፕሮጀክቱ ስራ ጥበቃና አማካሪዎችን መመደብና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ደግሞ በአክሲዮን ማህበሩ በኩል የሚተገበሩ እንደሆኑ በስምምነቱ ላይ ተመላክተዋል፡፡