13/03/2017
በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሴክተር ልማት ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት በሴክተሩ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ትላልቅ ፋይዳ ያላቸው ዘርፍ ዘለል የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ከትምህርትና ምርምር ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት ትኩረት ያደርጋል፡፡
በሴክተሩ የጥናትና ምርምር ሥራ አፈጻጸም ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በአጠቃላይ ስልቶች ላይ ለመወያየትና ለችግሮች መፍትሔ ለመፈለግ እንዲሁም በጀት የሴክተሩን የጥናትና ምርምር ሥራ ግብ ለማሳካት በተዘጋጁ ዕቅዶች ላይ በመነጋገር የአፈጻጸም ፕሮፖዛል ተዘጋጅቷል፡፡
በተጨማሪም ለሴክተሩ ጥናትና ምርምር ሥራ አፈጻጸም ሀገራዊ የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በመወያየት ግብአት የተሰባሰበ ሲሆን ከዩኒቨርስቲዎች ጋር ትስስርን ለማጠናከር ቀጠናዊ አደረጃጀቶችን ለማቋቋም እና ሴክተሩን የጥናት ምርምር ሥራ በቅንጅት ለመስራት የጋራ መግባባትን መፍጠር ያስቻለ የምክክር መድረክ ከጥር 2-4/2009 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ጌትፋም ሆቴል ተካሂዷል፡፡