01/04/2023
በልደታ ክ/ከተማ የወጣቶች ፌስቲቫል ተከፈተ።
ፌስቲቫሉ በወጣቶች አደባባይ በርካታ ወጣቶች በተገኙበት የተከፈተ ሲሆን የክ/ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅቶታል።
በፕሮግራሙ መልዕክት ያስተላለፉት የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ክብርዓለም ደምሴ እንደተናገሩት ወጣቶች ጊዜያቹህን አልባሌ ቦታ ከማሳለፍ ተቆጥባቹህ በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት በመገኘትን ለህይወታቹህ አስፈላጊ የሆኑ የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት አለባቹህ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ወጣቶች በቡኩላቸዉ እንደዚህ አይነት ፕሮግራሞች የወጣቱን ስነ-ምግባር በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ ሚና አላቸዉ ብለው ተግባሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።