17/05/2022
ኢትዮጵያን ከዓለም ለመነጠል የተደረገው ጥረት መክሸፉ ተገለጸ
*************************
ኢትዮጵያን ከዓለም ለመነጠል የተደረገው ጥረት መክሸፉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለፋት ዘጠኝ ወራት የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም በማስጠበቅ፣ ሉዓላዊነት መከበር፣ በጋራ ጥቅምና እኩልነት ላይ የተመሠረተ የውጭ ግንኙነት ማካሄድ፣ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እና ሁለንተናዊ የዳያስፖራ ተሳትፎን የትኩረት ማዕከል በማድረግ መሠራቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ አብራርተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል።
ውስጣዊ ችግሮች እና የኢትዮጵያን ከፍታ የማይሹ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት ዲፕሎማሲውን እጅጉ ፈትኖት እንደነበር ያነሱት አቶ ደመቀ፣ በኢትዮጵያውያን እና ወዳጅ ሀገራት ጥረት ኢትዮጵያን ከዓለም ለመነጠል የተደረገው ጥረት መክሸፉን ተናግረዋል።
ከአንዳንድ አካላት የሚመጡ ጫናዎች በተወሠነ የመለዘብ ሁኔታ ቢኖራቸውም አሁንም በተለያየ መልኩ መቀጠላቸውን እና ይህን ለመግታት ተጨማሪ ጥረቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ በተሻለ አቅም ለመሥራት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚያስችለውን ተቋማዊ አደረጃጀት እና አሠራር ማሻሻያ መተግበሩን እና የዲፕሎማሲ ሥራ ተፈላጊውን ክህሎትና ብቃት እንዲኖር ሥራዎች መሰራታቸው ተጠቁሟል።
የጎረቤት ሀገራትን ማዕከል ባደረገው የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ባለፋት ዘጠኝ ወራት በመሰረተ ልማት ትስስር እና የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትብብር ላይ ሥራዎች መከናወናቸው ተጠቁሟል።
Via..ኢቢሲ