16/07/2026
‹በሚተካው ደም የማይተካው ክቡር የሆነውን የሰው ህይወት እናድን› በሚል መሪ ሃሳብ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ወጣቶች ክንፍ ከ ወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎፍቃድ ጽ/ቤትጋር በጋራ በመሆን የደም ልገሳ መርሀ ግብር አካሂዷል ።
የደም ልገሳ መርሃ ግብሩ ላይ ቋሚ ደም ለጋሾች፣ የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴ እና አመራሮች ፣ የወጣት ክንፍ አባላት እንዲሁም የወረዳው ነዋሪ የተሳተፉበት እንደሆነ እና ዋና ዓላማውም አሁን ላይ በተለያየ አደጋዎችና በህመም እንዲሁም በወሊድ ምክንያት የሚከሰት ደም መፍሰስ የእናቶች ሞት ለማስቀረት የደም ልገሳው መርሃ ግብሩ መዘጋጀቱ ተገልጿል ።
በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው የወጣቶች ክንፍ ሰብሳቢ ወጣት ቃልኪዳን ዱፌራ
እንደተናገሩት ራሳቸውን ግባር ቀደም በማድረግ በፈቃደኝነት የተሞላ ደም መለገሳቸውን ጠቁመው ደም መለገስ የእናቶችን እና በተለያዩ አደጋ ተጋላጭ የሚሆኑ ዜጎችን መታደግ እና ህይወትን ማትረፍ መቻል በመሆኑ እጅግ ደስተኛ ሆነን ልንፈፅመው የሚገባ በጎ ተግባር ነው ብለዋል።
አክለውም ወጣት ቃልኪዳን ዱፌራ የደም ልገሳ ፕሮግራሙ ተሳታፊ ለሆኑ እና የስጦታዎች ሁሉ ውድ የሆነውን ደም የሠጡ ባለ ቅን ልቦችን በወረዳው ብልፅግና ፓርቲወጣቶች ክንፍ ስም ምስጋና ይድረሳችሁ ብለው በፈፀማችሁት ተግባር ሀገርና ህዝብ ያመሰግኗችኋልና ልትኮሩ ይገባችኋል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።