Lideta sub city health office

Lideta sub city health office HEALTH related

የልደታ ጤና ጣቢያ ባካሄደው የመጀመሪያ ቀዶ ጥገና አገልግሎት  አንዲት ወላድ  እናትን በተሳካ ሁኔታ ማዋለድ  እንደቻለ አስታወቀ።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 7/2018 ዓ.ምበልደታ ክፍለ ...
15/06/2026

የልደታ ጤና ጣቢያ ባካሄደው የመጀመሪያ ቀዶ ጥገና አገልግሎት አንዲት ወላድ እናትን በተሳካ ሁኔታ ማዋለድ እንደቻለ አስታወቀ።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 7/2018 ዓ.ም

በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ስር የሚገኘው የልደታ ጤና ጣቢያ ዛሬ ባካሄደው የመጀመሪያ ቀዶ ጥገና አገልግሎት አንዲት ወላድ እናትን በሰላም ማዋለድ በመቻሉ ወላዷንም እንኳን በሰላም ተገላገልሽ፣ ባለሙያዎችም አገልግሎቱን እንኳን በስኬት ፈጸማችሁ በማለት ለወረዳው ማህበረሰብ የእንኳን ደስ አላችሁ ምኞቱን የክፍለ ከተማው አስተዳደር ገልጿል።

የክፍለ ከተማው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን በየነ ስለተጀመረው አገልግሎት እንደገለጹት የቀዶ ጥገና ባለሙያዎቹ ያላቸውን እውቀት ተጠቅመው ወላድ እናትን በብቃት ማዋለድ በመቻላቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባ ገልጸዋል።

አክለውም እስከ አሁን ድረስ ጤና ጣቢያዎች በርካታ ወላዶች በሰላም ማዋለድ መቻላቸው እና አሁንም በልደታ ጤና ጣቢያ በአዲስ መልክ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩ የአገልግሎት አሰጣጡን ተደራሽነት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም ይህ የቀዶ ጥገና አገልግሎት መጀመሩ፣ ከዚህ በፊት አንዳንድ ወላድ እናቶች በሪፈር ምክንንያት ወደ ሆስፒታል ሄደው የሚገጥማቸው ድካምና እንግልት በማሰቀረት ወላድ እናቶችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል በመሆኑ ሁላችንም ደስ ብሎናል፤ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

የልደታ ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት በላብራቶሪ አገልግሎት የተሻለ አፈጻጸም ላመጡ ጤና ጣቢያዎች እውቅና ሰጠ።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 2/2018 ዓ.ምየልደታ ክ/ከተማ ጤና ፅ/ቤት በአዲሱ በአ...
09/06/2026

የልደታ ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት በላብራቶሪ አገልግሎት የተሻለ አፈጻጸም ላመጡ ጤና ጣቢያዎች እውቅና ሰጠ።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 2/2018 ዓ.ም

የልደታ ክ/ከተማ ጤና ፅ/ቤት በአዲሱ በአገር አቀፍ የላብራቶሪ ጥራት ምዘና መሠረት ባለ 5 ኮከብና ባለ 4 ኮከብ ደረጃ ያገኙ ጤና ጣቢያዎች በማመስገን እውቅና በየ ደረጃው ሰጠ።

ላብራቶሪዎች ለህክምና ጥራትና ውጤታማነት እጅግ ወሳኝ በመሆናቸው በየአመቱ በአገር አቀፍ የላብራቶሪ ጥራት ማረጋገጫ መስፈርት የሚመዘኑ ሲሆን በዚህ አመት እጅግ በተሻለና በተሟላ ሁኔታ ላይ በመድረሳችው ይህ ሽልማት በከተማ አስተዳደሩ ስር ከሚገኙ ጤና ጣቢያ ጋር ተወዳድረው ማሳካት ችለዋል።

ስለተገኘው ውጤት የክፍለ ከተማው ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መስፍን በየነ እንዳሉት በተዋረድ ከክ/ከተማ እስከ ጤና ጣቢያ ያሉ ቡድን መሪውችና ባለሙያዎች ሌት ተቀን በመልፋት የመጣ ውጤት ሲሆን ክፍለ ከተማውም የህክምና መሳሪዎችና አስፈላጊ ግብዐቶች እንዲሟሉ በማድረግ ከፍተኛ ድረሻ ተወጥቷል።

ባጠቃላይ ላብራቶሪዎቻችን የተሟሉና ጥራታቸው የጠበቁ በመሆናቸው አንድም ታካሚ ወደ ውጪ የሚላክ የሌለባቸውና ለሚሰጡት አገልግሎት ሁሉ በራሳቸው የተሟላ የላብራቶሪ አገልግሎት መስጠት የሚችሉበት ደረጃ ደረሰዋል።በመሆኑ ለመጣው ውጤት ለሁሉም ባለድረሻ አካል ባለሙያ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልኩ በቀጣይም ውጤተማነትን አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል ሃላፊው።

በመጨረሻም ለሁሉም ጤና ጣቢያዎች የዋንጫና የሰርተፊኬት ሽልማት የተሰጠ ሲሆን 5 ኮከብ ያገኘው ጀነራል ጃገማ ኬሎ የተለየ ሽልማትና እውቅና አግኝቷል።

በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ

ምስጋናም በየደረጃው🙏🙏🙏

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር  በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ምየልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት  አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ...
30/03/2026

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለዳ "ወርቃማው ሰኞ" የዕውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።

በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት እና ግንዛቤ የሰጡት አቶ ሳሙኤል ወርቁ ስለ SBFR እንዴት በቀላሉ የጤና ስራዎችንና የሚገጥሙ የስራ ማነቆዎችን ከስር ከስር እየለየ በመፍታት የተሻለ የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ ስለመሆኑ ሰፊ ግንዛቤ ተሰቷል።

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር  በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ምየልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት  አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ...
23/03/2026

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለዳ "ወርቃማው ሰኞ" የዕውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል ።

በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት እና ግንዛቤ የሰጡት የህክምና አገልገግሎት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን በትሩ ስለ managment and leadership እንዴት በምን መንገድ ስራዎችን መምራትና ማስተዳደር እንደሚቻል ሰፊ ግንዛቤ ሰተዋል።

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር  በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዶል፡፡ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 30/2018 ዓ.ምየልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለ...
09/03/2026

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዶል፡፡

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 30/2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለዳ "ወርቃማው ሰኞ" የዕውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።

ዘወትር ሰኞ ማለዳ የዕውቀት ሽግግር ፣ ተሞክሮ እና ግንዛቤ የምናገኝበት መሆኑን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በወ/ሮ አዲስ አለም ቦጋለ ስለ ሴቶች ቀን /march 8/ አስመልክት ለሰራተኛው ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን መረጃውን መለዋወጣችን በስራችን ላይ ውጤታማ ቀልጣፋ ብሎም ተከባብሮ ስራ የሚሰራበት በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጣችንን ላይ አወንታዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ግንዛቤ እንዲኖረን ያስችላል ብለዋል፡፡

የልደታ ክ/ ከተማ ጤና ጽ/ቤቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡት ጤና ጣቢያዎች የሽልማት እውቅና ሰጠ።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 13/2018 ዓ.ምየልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በ2018...
21/02/2026

የልደታ ክ/ ከተማ ጤና ጽ/ቤቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡት ጤና ጣቢያዎች የሽልማት እውቅና ሰጠ።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 13/2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት የ6 ወር አፈጻጸሙን ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ከገመገመ ቡኋላ በአፈጻጸማቸው የላቀ ውጤት አምጥተዋል ያላቸውን ጤና ጣቢያዎችን በሽልማት ዛሬ እውቅና ሰቷል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መስፍን በየነ በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት 6 ወራት ባብዛኛው የተሻለ የጤና አገልግሎት የሰጠንበት ቢሆንም የተወሰነ ክፍተትም ታይቷል ብለዋል። ሃላፊው ሲቀጥሉም በቀጣይ ጊዜያት የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ ከስር እስር እየተከታተሉ በመቅረፍ ህብረተሰቡን በከፍታ ማገልገል አለብን ብለዋል።

ለተሳታፊዎች ከመደረኩ የ2017 የ6 ወር ከ2018 በጀት አመት 6 ወር ጋር የነበረን አፈጻጸም በንጽጽር በማቅረብ የነበሩ ውጤቶችንና የታዩ ክፍተቶችን ለማሳየት ተሞክሯል። ተያይዞም የ6 ወር ቁልፍ ተግባራት ተለይተው ዝቅ ባሉት ላይ ዝቅ ያሉበት፣ የሚስተካከሉበት፣ ማን እና እንዴትመቼ መፈታት እንዳለባቸው አቅጣጫ ተሰቶባቸዋል።

ላለፉት 5 ተከታታይ ቀናት በዘመቻ ሲሰጥ የነበረው ከ9_14 አመት የልጅ አገረዶች የማህጸን በር ካንሰር ክትባት አፈጻጸሙ 100% ነው ተባለ።ል/ክ/ከተማ ጤና  ጽ/ቤት የካቲት 13/2018 ዓ...
20/02/2026

ላለፉት 5 ተከታታይ ቀናት በዘመቻ ሲሰጥ የነበረው ከ9_14 አመት የልጅ አገረዶች የማህጸን በር ካንሰር ክትባት አፈጻጸሙ 100% ነው ተባለ።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 13/2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በአስሩ ወረዳ፣ በ40 የመንግስትና የግል ት/ቤቶች ላይ እንዲሁም ከት/ቤት ውጪ ለሚገኙ ከ8ቱ ጤና ጣቢያዎች በተውጣጡ 10 የከታቢ ቡድኖች ከ9_14 አመት ለሆናቸው ሴቶች የክትባቱን ዘመቻ ያካሔደ ሲሆን ዘመቻውም ለ5 ቀናት ተሰቷል።

የማህጸን በር ካንሰር የዘመቻ ክትባት ለመከተብ በክፍለ ከተማው እንደ እቅድ የተያዙት 2663 ሴቶች ቢሆኑም
2265ዎቹ ሲከተቡ አፈጻጸሙም ከ100% በላይ ነው ተብሏል።

በዘመቻው ላይ እስካሁን የተሳተፉ፣ ያስተባበሩ እና አመራር የሰጡ ሁሉ የጤና ጣቢያ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማ አስተባባሪዎ፣ የትምህርት ጽ/ቤት አመራሮች እና የጤና ቢሮ ደጋፊዎች የሚዲያ አካላት እና የሐይማኖት ተቋማት በጽ/ቤቱ ተመስግነዋል።

የወርቃማዉ ሰኞ መርሃ ግብር ተካሄደ።   ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 9/2018 ዓ.ም የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት  ቡድን መሪና ሠራተኞች የወርቃማዉ ሰኞ መርሃ ግብር በፋረማሲ ቡድ...
16/02/2026

የወርቃማዉ ሰኞ መርሃ ግብር ተካሄደ።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 9/2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ቡድን መሪና ሠራተኞች የወርቃማዉ ሰኞ መርሃ ግብር በፋረማሲ ቡድን ሰራተኛ አቶ ኦሊያድ ንጉሴ በኩል ስለ አንቲ ማይክሮቢያል ሪዚስታንስ ላይ ሰፊ ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን ሰራተኛውም የተሳለ መረጃ አግኝቷል።

የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር  ክትባት በዘመቻ ሊሰጥ ነው።ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 6/2018 ዓ.ምከየካቲት 9_13/2018 ዓ.ም እድሜያቸው ከ9-14 አመት ለሞላቸው ልጅ አገረዶች በዘ...
13/02/2026

የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት በዘመቻ ሊሰጥ ነው።

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት የካቲት 6/2018 ዓ.ም

ከየካቲት 9_13/2018 ዓ.ም እድሜያቸው ከ9-14 አመት ለሞላቸው ልጅ አገረዶች በዘመቻ ለሚሰጠው የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ከትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለመምህራን እና ለተማሪ ወላጅ ተወካዮች የግንዛቤ መስጫ መድረክ ፈጠረ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን በየነ ለተሳታፊዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በአገራችን ከጡት ካንሰር ቀጥሎ የሴት እህቶቻችን የጤና ችግር ሲሆን ይህንን ታሳቢ በማድረግ በትምህርት ቤት ያሉ ከ9_14 አመት የሞላቸው ልጅ አገረድ ተማሪዎች ጤናቸው የተጠበቀና አምራች ዜጋ መሆን እንዲችል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው በጋራ ተናበን በመስራት እድሜያቸው የደረሰ ሴት ተማሪዎች ክትባቱን እንዲወስዱ ማድረግና ክትባቱን ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ግብዓቶችንና ምቹ ቦታዎችን ልናመቻች ይገባል ብለዋል።

ስለበሽታው ስርጭትና ተጋላጭነት በወ/ሮ አለም ቤኛ ከመድረክ ለተሳታፊዎች ቁጥራዊ መረጃ በሰፊው ሳይንሳዊ መረጃ ያቀረበች ሲሆን የበሽታውን መስፋፋት ለመግታት እንደጤና ሴክተር 3 ስትራቴጂዎች የተነደፉ ሲሆን 1ኛ. 90% ተጋላጭ ሴቶችን መከተብ፣ 2ኛ. 70% የማህፀን በር ካንሰር ልየታ ማድረግ እና 3ኛ. 90% ደግሞ የህክምና አገልግሎት መስጠት ናቸው ተብሏል።

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር  በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዶል፡፡ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ታህሳስ 27/2018 ዓ.ምየልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለ...
05/01/2026

የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዶል፡፡

ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ታህሳስ 27/2018 ዓ.ም

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች ዘወትር ሰኞ ማለዳ "ወርቃማው ሰኞ" የዕውቀት ሽግግር በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ተካሂዷል።

ዘወትር ሰኞ ማለዳ የዕውቀት ሽግግር ፣ ተሞክሮ እና ግንዛቤ የምናገኝበት መሆኑን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በአቶ አብዱልዋሂድ አብዶ ስለ google form አጠቃቀምና ለስራ አመቺነቱ ዙሪያ ለሰራተኛው ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን መረጃውን መለዋወጣችን በስራችን ላይ ውጤታማ ቀልጣፋ ብሎም ወረቀት አልባ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ የምንሆንበት በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጣችንን ላይ አወንታዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ግንዛቤ እንዲኖረን ያስችላል ብለዋል፡፡

Address

0115531533
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 17:00
Sunday 08:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lideta sub city health office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share