22/04/2026
የኢትዮጵያ ጂኦሎጅካል ኢንስቲትዩት ከቼክ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ።
(GIE)
# # # # # # #
(ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ጂኦሎጅካል ኢንስቲትዩት ከቼክ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ።
የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢጃራ ተስፋዬ እና የቼክ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ምክትል ዳይሬክተር ፔትር ሚክሳ ናቸው::
ስምምነቱ በኢትዮጵያ የጂኦሎጂካል ካርታ ዝግጅት ፣ ማዕድንና የጂኦተርማል ኢነርጂ ሀብት ፣ በጂኦሎጂካል ካርታ ዝግጅትና በስነ-ምድር አደጋ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ነው::
ሁለቱ ወዳጅ ሃገራት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በጋራ እንደሚሰሩ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢጃራ ተስፋዬ ስምምነቱ ለማዕድኑ ዘርፉ ከሚያበረክተው አስተዋፆ ባሻገር የትብብር ግንኙነታቸውን ለማጠናከርና ለጋራ ተጠቃሚነታቸው ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልፀዋል።
ይህ ስምምነት ከአውሮፓ ህብረት የሚደገፉ ፕሮጀክቶችን እንደ TAEIX እና PANAFGEO ጋር ተባብሮ ለመስራት ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
በዛሬው እለት በተደረገው የስምምነት መርሐ-ግብር የሁለቱ ሀገራት የዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/GIE2023E
Website:- https:www.gie.gov.et/
Telegram: - https://t.me/ethiopiangeology
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.