Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን

Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን Ensure smooth flow of information between the woreda Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information

Argoba communication

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የማሾ ግብይትና የእሴት ሰንሰለት ዙሪያ ወርክሾፕ ተካሄደኮምቦልቻ- ሰኔ 19/2018 ዓ/ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የማሾ ግብይትና የእ...
26/06/2026

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የማሾ ግብይትና የእሴት ሰንሰለት ዙሪያ ወርክሾፕ ተካሄደ

ኮምቦልቻ- ሰኔ 19/2018 ዓ/ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የማሾ ግብይትና የእሴት ሰንሰለት ማጠናከርን ዓላማ ያደረገ ወርክሾፕ በኮርዴይድ ኢትዮጵያ ድጋፍ በኮምቦልቻ ከተማ ተካሂዷል።

በወርክሾፑ የማሾ ምርት ከምርት እስከ ገበያ ያለውን የእሴት ሰንሰለት ማጠናከር፣ የገበያ ትስስርን ማሻሻል፣ የምርቱን ተወዳዳሪነት ማሳደግ እና ለአምራቾች የተሻለ የገበያ ዕድል መፍጠር ላይ ውይይት ተደርጓል።

የወርክ ሾፕ ተሳታፊዎችም የዘርፉን ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች በመለየት ለቀጣይ በቅንጅት ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የንግድ ቀን በዓል “ሕጋዊ፣ ተደራሽና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ሥርዓት እንገነባለን” በሚል መሪ ቃል ተከበረመዲና-ሰኔ 19/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በ...
26/06/2026

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የንግድ ቀን በዓል “ሕጋዊ፣ ተደራሽና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ሥርዓት እንገነባለን” በሚል መሪ ቃል ተከበረ

መዲና-ሰኔ 19/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት “ሕጋዊ ተደራሽና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ሥርዓት እንገነባለን” በሚል መሪ ቃል የንግድ ቀን በዓል ፓናል ወይይት ተከብሯል።

በበዓሉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ መሃመድ ሰይድ፣ የንግድ ማኅበረሰቡ በሕጋዊ የንግድ ሥርዓት ውስጥ በመሆን መስራት እንደሚገባ ገልጸው፣ ሕገወጥ የንግድ እንቅስቃሴንና የሸማቾችን ጥቅም የሚጎዳ ስግብግብ የንግዴን ባ በጋራ መታገል አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የወረዳው ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ሲስተር አሚናት ኑሩ በበኩላቸው ሕገወጥ ንግድን በመከላከል ሁሉም አካላት በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ገልጸው፣ ሕገወጥ ንግድ የሀገርን ኢኮኖሚ እና ሕጋዊ ነጋዴዎችን እንደሚጎዳ አስረድተዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የውሃና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ መሃመድ በበኩላቸው የንግድ ቀን ንግዱን የሚያጋጥሙ ማነቆዎች የሚለዩበትና መፍትሔ የሚፈለግባቸው ጠቃሚ መድረክ በመሆኑ በየዓመቱ ሊከበር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በወረዳው በሕጋዊ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የታየው መሻሻል እንዳለ ጠቅሰው፣ ይህንንም የበለጠ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

በውይይቱ ወቅት ተሳታፊዎች በንግድ ዘርፉ የመንግሥት ድጋፍ እና ትኩረት እንዲጠናከር የጠየቁ ሲሆን፣ ለተነሱ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም በወረዳው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ ነጋዴዎች እና ተቋማት የእውቅና እና የሽልማት ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ለ1,600 ተጋላጭ ወገኖች የሚውል 33 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተገምግሟልመዲና- ሰኔ 17/2018 ዓ.ም(አርጎባ ኮሙኒኬሽን )በአርጎባ  ብሄረሰብ...
24/06/2026

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ለ1,600 ተጋላጭ ወገኖች የሚውል 33 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተገምግሟል

መዲና- ሰኔ 17/2018 ዓ.ም(አርጎባ ኮሙኒኬሽን )

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ለአደጋ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚደረገውን ሰብአዊ ድጋፍ በውጤታማነት ለማስፈጸም የ1ኛው ዙር የዩኒሴፍ (UNICEF) የገንዘብ ድጋፍ ፕሮግራም የተጠቃሚዎች ምልመላና የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ግምገማ ተካሂዷል።

በግምገማው የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እንዲሁም የደቡብ ወሎ ዞን ልዑካን ቡድን ከአርጎባ ወረዳ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎች ጋር በመሆን በቢሮና በመስክ የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም የጋራ የሪቪው መድረክ አካሂደዋል።

በፕሮግራሙ በአጠቃላይ 33 ሚሊዮን ብር ለ1,600 አደጋ ተጋላጭ ወገኖች የሚውል ሲሆን፣ ተጠቃሚዎቹ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት በመጀመሪያና በሁለተኛ ዙር በቀጥታ ተለይተው ተመልምለዋል።

ልዑካን ቡድኑ ከወረዳው የሴቶች፣ ሕጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ባለሙያዎች ጋር በመሆን ባካሄደው የቢሮና የመስክ ምልከታ፣ የቅድመ ዝግጅት ሥራው በተቀመጠው ዓላማና አሰራር መሰረት መከናወኑን አረጋግጧል።

በግምገማው ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተለይተው የተወደሱ ሲሆን፣ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ጉዳዮችም በአስቸኳይ ተስተካክለው ወደ ዋናው የትግበራ ምዕራፍ እንዲገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በተጨማሪም ተጠቃሚዎች ስለሚደረግላቸው ድጋፍ፣ የክፍያ ሂደትና ገንዘቡን በተገቢው ዓላማ ለመጠቀም በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው የማስተዋወቅ ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸው ተጠቅሷል።

ልዑካን ቡድኑ ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ እንዲደርስ ለአበረከቱት አስተዋፅኦ ለአርጎባ ወረዳ አስተዳደር፣ ለአብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም ለሴቶች፣ ሕጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ምስጋና አቅርቧል።

የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ኑር በበኩላቸው ለተደረገው ሰብአዊ ድጋፍ ምስጋናቸውን ገልጸው፣ በወረዳው አሁንም በርካታ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖች እንዳሉ በማስታወስ፣ መሰል የሰብአዊ ድጋፍ ፕሮግራሞች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ አመራሮች  አፋር ተላላክ  አርጎባ መዲና መንገድ ስራን ምልከታ  አደረጉ ⬇️⬇️
24/06/2026

የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ አመራሮች አፋር ተላላክ አርጎባ መዲና መንገድ ስራን ምልከታ አደረጉ ⬇️⬇️

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመይጢ መስኖ የሙዝ ክላስተር የችግኝ ተከላ ስራ በይፋ ተጀመረመዲና - ሰኔ 17/2018 ዓ.ም (የአርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመይጢ መስኖ...
24/06/2026

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመይጢ መስኖ የሙዝ ክላስተር የችግኝ ተከላ ስራ በይፋ ተጀመረ

መዲና - ሰኔ 17/2018 ዓ.ም (የአርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመይጢ መስኖ የሙዝ ክላስተር ልማት የችግኝ ተከላ ስራ በይፋ ተጀምሯል።

ለሙዝ ተከላው አስፈላጊ የሆኑ የጉድጓድ ቁፋሮ፣ የመሬት ዝግጅትና ሌሎች የቅድመ ተከላ ስራዎች በተገቢው ሁኔታ ከተጠናቀቁ በኋላ፣ ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የወረዳው አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ኑር አብዱ፣ ሌሎች የወረዳ አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እንዲሁም የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የኤክስቴንሽን ቡድን መሪ በቦታው ተገኝተው የተከላ ስራውን በይፋ አስጀምረዋል።

በመርሃ ግብሩ የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የኤክስቴንሽን ቡድን መሪ ለአርሶ አደሮች በሙዝ አመራረት፣ በችግኝ ተከላ ሥነ-ዘዴ፣ በእርቀት አያያዝና በእንክብካቤ ዙሪያ ሙያዊ ምክርና ድጋፍ በመስጠት የልማቱ ውጤታማነት እንዲጠናከር አስፈላጊ መመሪያዎችን አስተላልፈዋል።

በመይጢ መስኖ ክላስተር ከ200 ሄክታር በላይ መሬትን በሙዝ ልማት ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህ የክላስተር ልማት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ በማድረግ የምርት መጠንና ጥራትን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም የልማት ስራው በተያዘለት እቅድ መሰረት ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በጥንቃቄ መከናወናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የችግኝ ተከላው በይፋ መጀመሩን ተከትሎ የተከላ ስራው በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል ከወረዳው ግብርና የተገኘው መረጃ ያመለክታል

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ በተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ለቀበሌ አመቻች ቡድኖች ስልጠና ተሰጠመዲና - ሰኔ 16/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔ...
23/06/2026

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ በተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ለቀበሌ አመቻች ቡድኖች ስልጠና ተሰጠ

መዲና - ሰኔ 16/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የፕላንና ልማት ጽሕፈት ቤት በተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ለቀበሌ አመቻች ቡድኖች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

ስልጠናው ማህበረሰቡን በዕቅድ ዝግጅትና በልማት ሂደት ማዕከል ያደረገ፣ ፍላጎቱንና ቅድሚያ ፍላጎቶቹን የሚያንጸባርቅ እንዲሁም በወረዳው የልማት ሥራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ የሚያረጋግጥ ዕቅድ ለማዘጋጀት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መሃመድ ሰይድ እንደገለጹት፣ እየተዘጋጀ ያለው ዕቅድ በወረዳው የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችልና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በተግባር የሚያረጋግጥ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

አቶ መሃመድ አክለውም ዕቅዱ በተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅትና ትብብር በማጠናከር የልማት ሥራዎችን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።

የሚዘጋጀው ዕቅድም የወረዳውን የልማት ጉዞ ወደ ተሻለ ደረጃ በማሸጋገር የህዝቡን ተጠቃሚነት እንዲያጎለብት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

በስልጠናው ላይ የተገኙት የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የውሃና ኢነርጂ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ መሃመድ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሚዘጋጀው ዕቅድ ቀበሌዎችን በተጨባጭ ሊቀይር የሚችል፣ የማህበረሰቡን እውነተኛ ፍላጎት መሰረት ያደረገና በተግባር ሊፈጸም የሚችል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ከማቀድ ባሻገር ዕቅዶችን በጥራት መተግበር፣ በተናበበ መልኩ መከታተልና ውጤታማ ማድረግ የሁሉም አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ የቀበሌ አመቻች ቡድኖች በየቀበሌያቸው የሚከናወነውን የአሳታፊ ዕቅድ ዝግጅት በተሻለ ጥራት ለመምራት የሚያስችላቸውን ዕውቀትና ክህሎት ማግኘታቸው ተገልጿል። በቀጣይም ማህበረሰቡን በስፋት በማሳተፍ ተጨባጭና ዘላቂ የልማት ውጤቶችን ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ተጠቁሟል።

ስልጠናው በንድፈ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ ልምምዶች፣ በቡድን ውይይቶችና በልምድ ልውውጥ የታገዘ ሲሆን፣ ተሳታፊዎች በቀጣይ በየቀበሌያቸው የሚያካሂዱትን የአሳታፊ ዕቅድ ዝግጅት በብቃትና በተቀናጀ መንገድ ለመምራት የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ ማስቻሉ ተገልጿል።

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ በመዲና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት  የችግኝ ጉድጓድ ተዘጋጀ መዲና-ሰኔ 16/2018 ዓ.ም(አርጎባ ኮሙኒኬሽን)  በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የመዲና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት...
23/06/2026

በአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ በመዲና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የችግኝ ጉድጓድ ተዘጋጀ

መዲና-ሰኔ 16/2018 ዓ.ም(አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ የመዲና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን በማስመልከት መምህራንና ተማሪዎች የችግኝ ጉድጓድ ዝግጅት ዘመቻ አካሂደዋል።

በዘመቻው ከ650 በላይ የችግኝ ጉድጓዶች የተዘጋጁ ሲሆን፣ በትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ ጥቅም የማይሰጥ ክፍት መሬት እንዳይኖር በማለት የተዘጋጀ መርሃ ግብር መሆኑ ተገልጿል።

የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አሊ ሰይድ በፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉ መምህራንና ተማሪዎችን አመስግነው፣ መጪው ዕረፍት ለሁሉም የሰላምና የፍቅር ጊዜ እንዲሆን ተመኝተዋል።

በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳ ለችግር ተጋላጭ ወገኖች የሚደረገው የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ የታላሚዎች ልየታ  አፈጻጸም ተገመገመመዲና - ሰኔ 15/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)በአርጎባ ብሔረሰብ ...
22/06/2026

በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳ ለችግር ተጋላጭ ወገኖች የሚደረገው የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ የታላሚዎች ልየታ አፈጻጸም ተገመገመ

መዲና - ሰኔ 15/2018 ዓ.ም (አርጎባ ኮሙኒኬሽን)

በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳ በግጭትና በድርቅ ለተጎዱ እንዲሁም ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሰጠውን የድንገተኛ ጊዜ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ታላሚዎች ልየታ አፈጻጸም የወረዳው ስቲሪንግ ኮሚቴ ገምግሟል።

በዩኒሴፍ (UNICEF) የገንዘብ ድጋፍ የሚተገበረው ይህ ፕሮጀክት፣ በተለይም በአንድ ወላጅ ለሚተዳደሩ ቤተሰቦች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና ለአረጋውያን ቅድሚያ በመስጠት የኑሮ ጫናቸውን ለማቃለልና የመግዛት አቅማቸውን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የድጋፉ አሰጣጥ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነትን ባማከለ መንገድ እንዲፈጸም የወረዳው ስቲሪንግ እና የቴክኒክ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ስራ መግባታቸው ተገልጿል።

በአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ የታላሚዎች ልየታ ሂደት በወረዳው ስቲሪንግ ኮሚቴ በዝርዝር የተገመገመ ሲሆን፣ ለቀጣይ የድጋፍ ስርጭት ሂደት አስፈላጊ አቅጣጫዎች መቀመጣቸው ተጠቁሟል።

የግምገማ መድረኩን የመሩት የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ መሃመድ ኑሩ የድጋፉ ተጠቃሚዎች ልየታ በተቀመጡ መስፈርቶች መሠረት ፍትሃዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነትን ባረጋገጠ መንገድ እንዲጠናቀቅ እንዲሁም በቀጣይ የድጋፍ አሰጣጥ ሂደትም ተመሳሳይ መርሆዎች በጥብቅ እንዲከተሉ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።

የድጋፍ ጥሪ‼"የብዙዎችን ልጆች ያስተማረች መምህር… ዛሬ ግን የእኛን እጅ ትጠብቃለች!""ሰውን የሚያኖረው ለሌላው የሚያደርገው በጎ ነገር ነው።"ይህ የገነት ይማም አህመድ ታሪክ ነው፤ የትጋት...
22/06/2026

የድጋፍ ጥሪ‼

"የብዙዎችን ልጆች ያስተማረች መምህር… ዛሬ ግን የእኛን እጅ ትጠብቃለች!"

"ሰውን የሚያኖረው ለሌላው የሚያደርገው በጎ ነገር ነው።"
ይህ የገነት ይማም አህመድ ታሪክ ነው፤ የትጋት፣ የክብር፣ የፈተና እና ዛሬ ደግሞ የተስፋ ታሪክ።

ገነት ይማም አህመድ በመካነሰላም ወረዳ 01 አሜጃ ቀበሌ ተወልዳ ትምህርቷንም በዚያው ተምራለች። ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በአርጎባ ብሔረሰብ ልዩ ወረዳ በመምህርነት ሙያ በብዙ ሕፃናት ሕይወት ላይ ዕውቀትን በመዝራት አገሯን በታማኝነት አገልግላለች።

ነገር ግን ሕይወት ሁልጊዜ በፈለግነው መንገድ አትሄድም። በገጠማት የጤና ችግር ምክንያት ከምትወደው የመምህርነት ሙያ ተለይታ፣ በወረዳው ሲቪል ሰርቪስ መሥሪያ ቤት በጽዳትና ተላላኪነት ሥራ ተመድባ ኑሮዋን በክብር መግፋት ቀጠለች።
ከእሷ ጋር የሠሩ ሁሉ አንድ ነገር ይመሰክራሉ፤ "ገነት በሥራዋ ታማኝ፣ በባህሪዋ ትሑት፣ በሰውነቷ ደግ ሴት ናት።"

ዛሬ ግን…
ዛሬ ገነት በከባድ የአእምሮ ሕመም እየተሰቃየች ትገኛለች። ሕመሙ እየበረታባት በመምጣቱ መሥራት ቀርቶ ራሷን እንኳን መንከባከብ እየከበዳት ነው።

ከዚህም በላይ የሚያሳዝነው በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ አጠገቧ ቆሞ "አይዞሽ" የሚላት፣ የሚያስታምማትና የሚያግዛት የቅርብ የቤተሰብ የላትም።

እጅ ከመዘርጋት ይልቅ ለመሥራት የመረጠች ሴት
ምንም እንኳን ሕመሙ እያሰቃያት ቢሆንም ገነት ልመናን አልመረጠችም ነበር።

የ200 ብር የማይሞላ ብስኩትና የሕፃናት ማስቲካ ገዝታ መንገድ ላይ ዘርግታ ለመሸጥ ትሞክራለች።
ነገር ግን የምታገኘው ገቢ ለጤናዋ ለመጣር ይቅርና ለዕለት ጉርሷ እና ለቤት ኪራይዋ እንኳን ሊሆን አልቻለም ።

ትናንት የሌሎችን ልጆች ያስተማረች፣ በታማኝነት አገልግላ የኖረች ይህች እኅታችን ዛሬ የእኛን ድጋፍ ትፈልጋለች።

የእያንዳንዳችን ትንሽ ድጋፍ ተደምሮ ለገነት ትልቅ ተስፋ ሊሆን ይችላል። አነስተኛ የንግድ ሥራ እንድትጀምር፣ ሕክምናዋን እንድትከታተል እና መኖር እንድትቀጥል ሰበብ እንሁናት እንርዳት‼ እንገዛት ‼
" የኛ ትንሽ እርዳታ ለገነት አዲስ ሕይወት ሊሆን ይችላል።"

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
ገነት ይማም አህመድ (Genet Yimam Ahmed)

የአካውንት ቁጥር፦ 1000494272397

🙏 መርዳት ባንችል እንኳን፣ ይህን መልዕክት በማጋራት (Share) ሌላ ሰው የገነት የተስፋ ምክንያት እንዲሆን ያድርጉ‼

"አንድ ሰውን መርዳት ዓለምን መቀየር ላይመስል ይችላል፤ ነገር ግን ለዚያ ሰው ዓለሙን ሙሉ መቀየር ነው።"

እንኳን ደስ አላችሁ!!በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ቃሉ 1 የምርጫ ክልል ላይ ለክልል ም/ቤት የተወዳደሩት ክብርት ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋየ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት አሸናፊ ሆነ...
21/06/2026

እንኳን ደስ አላችሁ!!
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ቃሉ 1 የምርጫ ክልል ላይ ለክልል ም/ቤት የተወዳደሩት ክብርት ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋየ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት አሸናፊ ሆነዋል።

Adres

Dessel

Website

Meldingen

Wees de eerste die het weet en laat ons u een e-mail sturen wanneer Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን nieuws en promoties plaatst. Uw e-mailadres wordt niet voor andere doeleinden gebruikt en u kunt zich op elk gewenst moment afmelden.

Contact De Organisatie

Stuur een bericht naar Argoba Communication-አርጎባ ኮሙኒኬሽን:

Delen